ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
129

በምዕራብ ጎጃም ዞን  የቡሬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ የሚገኘውን  ቁርጥራጭ ብረታብረት  በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የጨረታውን መስፈርቶች የምታሟሉ   መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን / ያላቸው፤ ከ200‚000.00/ሁለት መቶ ሽህ/ ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ  ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢንድ ቦንድ / ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ ግዥውን ግምታዊ ዋጋ መሰረት በማድረግ 20‚000.00 (ሃያ ሽህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ /ሲ.ፒ.ኦ / በኮሌጁ ስም ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስያዝ አለባቸው፡፡
  6. የጨረታ መቆያ ጊዜ ከ22/11/2016 እስከ 06/12/2016 ዓ.ም ለ15 ተከታታይ ቀናት ብቻ ይሆናል ፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን አንድ ወጥ በሆኑ የጨረታ መወዳደሪያውን ሰነድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቡሬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግዥ ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 07/12/2016 ዓ.ም 4፡00  ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታው የሚዘጋበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት በ16ኛው ቀን ማለትም በ07/12/2016 ዓ.ም ሲሆን ከረፋዱ 4፡00 የጨረታ ሳጥን ታሽጎ ተጫራቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት  በ07/12/2016 ዓ.ም  በእለቱ 4፡30  ጨረታው የሚከፈት ሁኖ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው በሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  9. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 774 07 71 ደውሎ ወይም በአካል ቀርቦ ማየት ይቻላል፡፡
  10. አሸናፊው ድርጅት ውል ከያዘ በኋላ የሚጠበነቅበትን ክፍያ በመክፈል ንብረቱን መረከብ ይኖርበታል፡፡
  11. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
  12. በጨረታው አሸናፊ የሆነ ድርጅት /ግለሰብ/ ማሸነፉ ከተገለፀ ከአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ውል ካልያዘ የጨረታ ማስከበሪያው ውርስ ይሆናል ፡፡
  13. ሌሎች በዚህ ማስታወቂያ ያልተገለፁ ነገሮች ካሉ በግዥ መመሪያው  መሰረት ተግባራዊ  ይሆናሉ፡፡
  14. አሸናፊው ድርጅት /ግለሰብ/ የሚዛን እና ሌሎች ወጭዎች በራሱ ሂሳብ ይሆናል፡፡
  15. የጨረታ ሰነዱን በኮሌጁ ግ/ፋ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 የማይመለስ 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ   ይቻላል፡፡

የቡሬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here