ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
69

ለሐዲስ አለማየሁ ልዩ አዳሪ ት/ቤት በ2017 በጀት አመት አገልግሎት የሚሰጡ እቃዎች ማለትም ሎት 1 ለተማሪዎች ምግብ የሚሆን ሰርገኛ ጤፍ ፣ሎት 2 የተማሪዎች ምኝታ ፍራሽ እና ሎት 3 የቢሮ እና የተማሪዎች መገልገያ ፈርኒቸር  በግልጽ ጨረታ  አወዳድሮ ለመግዛት እና ለማሰራት  ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ፡-

  1. የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
  3. የግብር መለያ ቁጥር (ቲን )ያላቸው፡፡
  4. የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም ያላቸው፡፡
  5. የጠቅላላ ግዥ መጠን ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  6. ማንኛውም ግዥ ከብር 10000 (አስር ሺህ ብር) በላይ 2 በመቶ ቅድመ ግብር ተቀንሶ የሚቀር ይሆናል፡፡
  7. የጨረታ ማስከበሪያ ከታወቁ ባንኮች /በሲፒኦ/ አንድ በመቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8. የጨረታ አሸናፊው የጨረታ ውል ማስከበሪያ ማሸነፋቸው በተገለፀ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከባንኮች የጠቅላላ ግዥ ዋጋ 10 በመቶ /ሲፒኦ/ በማቅረብ ውል መያዝ አለበት፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ላይ ህጋዊ ማህተም በማድረግ ፣የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና ቲን ነበር በአንድ በታሸገ ፖስታ አድርገው ት/ቤቱ ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
  10. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት እስከ 11፡30 የሥራ ሰዓት ይቆያል፡፡
  11. ጨረታው በቀን 26/09/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ይታሸጋል፡፡
  12. ጨረታው ተጫራቾች (ህጋዊ ወኪሎቻቸው) በተገኙበት በቀን 26/09/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ይከፈታል፡፡
  13. አሸናፊ ተጫራች ምርቱን /እቃውን/ በራሱ የትራንስፖርት ወጪ ት/ቤት ግቢ ድረስ ማቅረብ አለበት፡፡
  14. ት/ቤቱ ጨረታውን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. ከዚህ በላይ ያልተጠቀሱ የጨረታ መመሪያዎች በግዥ መመሪያ ቁጥር 1/2003 መሰረት ተግባራዊ የሚደረጉ ይሆናል፡፡

አድራሻ ፡- ደ/ማርቆስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ግቢ ስልክ 09 20 50 43 80 /09 20 50 68 87 /09 37 37 28 10 ደውለው መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የሐዲስ አለማየሁ ልዩ አዳሪ ት/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here