ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
60

የነፋስ መውጫ ሆስፒታል የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ ማንኛውም ተጫራች መወዳደር የሚችል መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘርፉ በ2017 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማስረጃ ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙትን ዕቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ስራ ሂደት ቢሮ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ  በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ጥሬ ገንዘብ በመሂ/1 በመቁረጥ ማስያዝ ፤ያስያዙበትን መሂ/1 ኮፒ ወይም  /ሲፒኦ/  ኦሪጅናሉን ከጨረታ ሰነዱ ጋር በፖስታ አሽገው ማስገባት አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የመጫረቻ ሰነዱን በጥንቃቄ ታሽጎ ፖስታው ላይ ፊርማና ማህተም ተደርጎ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ስራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 11፡00 ማስገባት ይችላሉ፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ስራ ሂደት ቢሮ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ጨረታውን ለመክፈት የሚገድብ ነገር አይኖርም፡፡
  10. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይታ ይኖረዋል፡፡ በ16ኛው ቀን 3፡30 ታሽጎ በዚሁ ዕለት 4፡00 ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በዚሁ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  11. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ስራ ሂደት ቢሮ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 445 08 87 /09 30 03 34 13 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. የጨረታ አሸናፊ የሚለየው በጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረበውን ሲሆን የሁሉም ዕቃዎች ዋጋ መሞላት አለባቸው፡፡
  14. ሆስፒታሉ ከአሸናፊው ተጫራች ላይ 30 በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብት አለው፡፡
  15. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈበትን ዕቃ ከሆስፒታሉ ድረስ ማቅረብ አለበት፡፡

የነፋስ መውጫ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here