ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
90

የፍኖተ ሰላም ከተማ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት ለመ/ቤቱ አገልግሎት የሚዉል የተለያዩ ዕቃዎችን ማለትም ሎት 1. ቧንቧና መገጣጠሚያ አገልግሎት በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል:: ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
  3. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ ቲን/ ያላቸዉ፡፡
  5. የግዥዉ መጠን ከብር 200‚000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ለሆነ ተጨማሪ  እሴት ታክስ /ቫት/ የተመዘገቡ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
  6. የተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ. ወይም በዉሃ አገልግሎቱ  ደረሰኝ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  7. ተጫራቾች ከ 1-5 የተዘረዘሩትን ማረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ::
  8. የጨረታ ማስታወቂያዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ ይዉላል፡፡ በ15ኛዉ ቀን 11፡30 ሳጥኑ ይታሸጋል፡፡ በ16ኛዉ ቀን ከጧቱ 3፡30  ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ቢገኙም ባይገኙም ጨረታዉ በግልጽ ይከፈታል፡፡
  9. ማንኛዉም ተጫራች ሀሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀዉ  የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰአት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. በተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማስገባት አይቻልም::
  11. የጨረታ መክፈቻዉ ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለዉ  የስራ ቀን  በተመሳሳይ  ሰዓት ይከፈታል፡፡
  12. በጨረታዉ ለተሸነፉ ተጫራቾች ከአሸናፊዉ ጋር ዉል እንደተያዘ የጨረታ ማስከበሪያዉ ይመለሳል፡፡
  13. ተጫራቾች የማይመለስ ብር ለእያንዳንዳቸው ብር 200/ ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 2 ዘወትር በስራ ሰዓት መዉሰድ ይችላሉ፡፡
  14. አሸናፊዉ ተጫራች ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ ያሸነፈበትን የሎት ዕቃዎች ጠቅላላ ዋጋ የዉል ማስከበሪያ ዋስትና የሚሆን 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ /በጥሬ ገንዘብ/ ለፍኖተ ሰላም ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገ/ጽ/ቤት አስይዘዉ ዉል በመፈጸም ያሸነፉትን ዕቃ ፍ/ሠ/ከ/ዉ/ፍ/ አገ/ጽ/ ቤት ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸዉ፡፡
  15. ተመሳሳይ የሆኑ እቃዎች በአንድ ምድብ /ሎት/ በማድረግ ዉድድሩ የሚገለጸዉ በጠቅላላ የድምር ዉጤት ነዉ፡፡
  16. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  17. በጨረታዉ መሰረዝ ምክንያት ተጫራቾች ላወጡት ወጪ መ/ቤቱ ኃላፊነትን አይወስድም፡፡
  18. ለበለጠ መረጃ በስ/ቁ 0587751387/0075 /0923426123 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የፍኖተ ሠላም ከተማ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት

 

 

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here