ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
109

የመቄት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለመቄት ወረዳ እንስሳት ሀብት ልማት ተጠሪ ጽ/ቤት በተዘዋዋሪ ፈንድ በጀት በሎት ድምር ለእንስሳት ህክምና አገልግሎት የሚውል መድሃኒት መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ መወዳደር ለምትፈለጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባችኋል፡-

  1. ቲን ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  2. የሙያ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  3. ግዥው ከ200,000.00 /ከሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
  4. ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ አንድ በመቶ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  6. የውል ማስከበሪያ አስር በመቶ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 ማስያዝ የሚችሉ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  7. በጨረታ ሰነዱ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ የሌለው መሆን አለበት፡፡
  8. የጨረታ መክፈቻው ቀን ካላንደር ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ ቀጣይ ባሉት የሥራ ቀናት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  9. የጨረታ ሰነዱን ኮፒና ኦርጅናል በመለየት በሰም በታሸገ ፖስታ ማስገባት የሚችሉ በሰም የታሸገ ቢሆን ይመረጣል ባለመታሸጉ ግን ጨረታውን ውድቅ አያደርገውም፡፡
  10. ጨረታው በአየር ላይ የሚቆየው ከ06/12/2016 ዓም ጀምሮ እስከ 20/12/2016 ዓ.ም ለተከታታይ 15 የሥራ ቀናት እስከ 11፡30 የጨረታ ሰነዱ ይሸጣል፡፡
  11. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን በ21/12/2016 ዓም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ 3፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ ይከፈታል፡፡
  12. መስፈርቱን የምታሟሉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን መ/ወ/ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ደ/የስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 13 በመቅረብ የማይመለስ 00 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ ለሁሉም ሰነዶች በመክፈል መግዛት የምትችሉ ሲሆን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰርዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

ማሳሰቢያ፡- የጨረታ ሰነዱ የሚገባው ግ/ን/አስ/ደ/የስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 13 በሚገኘው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡  ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 033 211 00 91 ወይም 033 211 00 91 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የመቄት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here