ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
91

የምዕራብ በለሣ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓ.ም ለምዕራብ በለሣ ወረዳ ት/ጽ/ቤት በአልማ በጀት ለአርባያ ከተማ የአፀደ ህፃናት መማሪያ ብሎክ 1 /አንድ ብሎክ/ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ይህን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች /ድርጅቶች/ እንድትወዳደሩ እየጋበዝን፡- ስለሆነም በዚህ መሠረት ለመወዳደር ፍላጎት ያላችሁ ሁሉ፡-

  1. በዘመኑ የታደሠ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  3. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. ደረጃ 8 የሆኑ፡፡
  5. ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ቀን 23/10/2017 ዓ.ም እስከ 22/11/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 30 ቀናት እስከ 11፡30 ድረስ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ሥርስ ድልዝ ሣይኖረው በመሙላት በሁለት ፖስታ ማለትም ኦርጅናልና ኮፒ በማለት በጉልህ በፖስታው ላይ በመፃፍ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ክብ ማህተም ፣አድራሻ ፣ስልክ ቁጥር መፃፍ አለባቸው፡፡
  7. ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በተዘጋጀው ሣጥን በ23/11/2017 ዓ.ም 3፡30 ታሽጎ በ4፡30 ላይ በግልጽ ይከፈታል፡፡
  8. ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከፊት ለፊቱ ልዩ ፊርማውን ማስቀመጥ ይኖርባቸል፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ /ሲፒኦ/ ከጠቅላላ የጨረታ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋጋጠ ቼክ ወይም በጥሬ ገንዘብ ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ለእለት ገንዘብ ያዥ ገቢ በማድረግ የገቢ ደረሠኙን ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሠነድ ጋር አያይዞ ጨረታ ሣጥኑ ከኦርጅናል ሠነድ ጋር ማስገባትአለባቸው፡፡
  10. አሸናፊው ተጫራች የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ በጨረታ ውጤት ከታወቀ የመድን ድርጅት የሚቀርብ በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ በባንክ ቸክና ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ገቢ ያደረጉበትን ኮፒ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  11. ለበለጠ መረጃ ከፈለጉ ምዕ/በ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በስልክ ቁጥር 09 18 71 19 47 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ጨረታው በክልሉ ገ/ኢ/ል ቢሮ ባወጣው የግዥ መመሪያ የሚተዳዳር ይሆናል፡፡
  14. የጨረታ ሰነዱን ምዕ/በ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ከረዳት ገንዘብ ያዥ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ መግዛት ይችላ፡፡

የምዕራብ በለሣ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here