ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
117

በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የበላይ ዘለቀ ክ/ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት ዓመታዊ መስተንግዶ፣ ህትመት እና ኤሌክትሮኒክስ ጥገና በግልጽ የጨረታ የግዥ ዘዴ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
  3. በስማቸው የታተመ ደረሰኝ ያላቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰረተ /ሲፒኦ/ የሞሉትን ዋጋ አንድ በመቶ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  6. የድርጅቱ ሕጋዊ ማህተምና የሞላው ሰው ስምና ፊርማ መኖር አለበት፡፡
  7. አሸናፊው የሚለየው በአጠቃላይ በዋጋ ድምር ይሆናል፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ የአሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ ከ200,000.00 /ከሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆኑ የቫት ተመዝጋቢነት መረጃ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  9. የእያንዳንዳቸው ሎቶች ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዟል፡፡
  10. ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያቀረቡትን /የሞሉትን/ ዋጋ በፖስታ በማሸግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ቢሮ ቁጥር 06 ማስገባት ይችላሉ፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወጥ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ከ06/12/16 ዓ.ም እስከ 26/12/2016 ዓ/ም ድረስ በግዥ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 06 ዘውትር በሥራ ሰዓት የሚቆይ ሆኖ በ27/12/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ 4፡00 እጩ ተወዳዳሪዎች /ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  12. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 06 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  14. ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 226 58 52 ወይም በበላይ ዘለቀ ክ/ከተማ ቢሮ ቁጥር 06 በአካል በመምጣት መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  15. ማሳሰቢያ፡- የጨረታው አሸናፊ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል እና ተቋሙ ድረስ መጥቶ አገልግሎት መስጠት የሚችል መሆን አለበት፡፡

የበላይ ዘለቀ ክ/ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here