በማዕላዊ ጎንደር ዞን ጣቁሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ሥር ባሉት የፑል ንብረት ክፍል ያሉ ቁርጥራጭ ብረቶችና የመኪና ቦዲ ዕቃዎች ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ማንኛውም ግለሰብ ድርጅት በጨረታው የመሳተፍ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች የንብረቶችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ ከጽ/ቤቱ ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 05 በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከ 14/11/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት እና በ16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚወዳደሩበትን የዕቃ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም ከ60 (ስልሳ) ቀን ያላነሰ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ወይም በጥሬ ገንዘብ በመምሪያው የገቢ ደረሰኝ የተቆረጠ በመምሪያው ሥም ማሥያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን /መጫረቻውን/ ዋናውን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማሸግ ቢሮ ቁጥር 05 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ስዓት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 05 በ16ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ይከፈታል፡፡
- የመክፈቻ ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሣሣይ ስዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ለሽያጭ የቀረቡ ንብረቶችን በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ላይ በተገለፀው ቦታ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ ንብረቶች በአሉበት ንብረት ክፍል በመሄድ በአካል ማየት ይቻላል፡፡
- ጨረታውን አሸናፊ የሚሆነው ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ፖስታቸው ላይ ሥም ፊርማ ፣ሥልክ ቁጥር መፃፍ አለባቸው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 336 448 ወይም 09 09 36 76 39 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡- ጣቁሳ ወረዳ ደልጊ ገንዘብ ት/ቤት ይገኛል፡፡
የጣቁሳ ወረዳ ደልጊ ገንዘብ ት/ቤት