ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
40

የአለፋ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በወረዳዉ ዉስጥ ባሉ ንብረት ክፍሎች ዉስጥ የተለያዩ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች ያሉ መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልጉ ማንኛዉም ግለሰብ /ድርጅት/ በጨረታዉ የመሳተፍ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  2. ተጫራቾች የንብረቶችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ በጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 1000 /አንድ ሺህ ብር/ ከወረዳዉ ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 02 በመክፈል ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ ም ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት እና በ16ኛዉ ቀን 4፡00 ድረስ የጨረታ ሰነዱን መዉሰድ ይቻላል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚወዳደሩበትን የእቃ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም ከ60 ቀን ያላነሰ በሁኔታ ላይ ያልተመሰተ የባንክ ዋስትና ወይም /ቢድ ቦንድ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ የገቢ ደረሰኝ የተቆረጠ በወረዳዉ ስም ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  5. ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን /መጫረቻዉን/ ዋናዉን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማሸግ ቢሮ ቁጥር 03 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛዉ ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች ወይም በህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 03 በ16ኛዉ ቀን 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ይከፈታል፡፡
  7. የመክፈቻ ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣይ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  8. ተጫራቾች ለሽያጭ የቀረቡ ንብረቶችን በተዘጋጅዉ የዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ላይ በተገለጸዉ ቦታ ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛዉ ቀን 4፡00 ድረስ ንብረቶች ባሉበት የንብረት ክፍል በመሄድ በአካል ማየት ይቻላል፡፡
  9. የጨረታዉ አሸናፊ የሚሆነዉ በከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች ፖስታቸዉ ላይ ስም ፣ፊርማ ፣ስልክ ቁጥር መጻፍ አለባቸዉ፡፡
  11. ለበለጠ መረጃ 058 270 01 95 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  12. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡

የአለፋ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here