ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
68

ቁጥር 1/2018

በአብክመ  ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም በጀት አመት ሎት 1 የመኪና አመታዊ ጥገና ፣ሎት 2 የመፅሄትና ጋዜጣ ግዥ እና ሎት 3 የአንሶላ ፣ብርድ ልብስ የመኪና ወንበር ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዥ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘርፉ እና ዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ከግዥ ፣ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 33 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የግዥ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 2 በመቶ (ቢድ ቦንድ) በጨረታ ሠነዱ የተገለፀውን የብር መጠን በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት በተሰጠ ሕጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ይኖርባቸዋል። ጨረታዉም በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ግዥ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ፋይ/ንብ/አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጐ በዚሁ ቀን 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ይሁን እንጂ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጽ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 30 በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058 220 10 68 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 20 30 /058 220 10 81 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

ባሕር ዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here