ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
43

በቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግ/ን/አስ/ቡድን በወረዳው ለሚገኙ ሴ/መስሪያ ቤቶች ለ2018 የበጀ ዓመት አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 መኪና መለዋወጫ  እቃዎች ፣ ሎት 2  መኪና ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ አሸናፊዎችን ለይቶ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ እና በዘርፍ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2.  የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3.  የግዥው መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆናችሁን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  1. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  2. ተጫራቾች የሚፈለጉትን የእቃ አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊክሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 04 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ  የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በባንክ ዋስትና በመሂ 1  በጥሬ ገንዘብ የተቆረጠ ደረሰኝ ኮፒ አድርገው በፖስታ አሽገው ማስገባ አለባቸው፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ቋራ ወረዳ ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 04 ከ28/11/2017 እስከ  12/12/2017 ዓ.ም 12፡00 ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቋራ ወረዳ ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥኑ በቀን 13/12/2017 ዓ/ም 3፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡ በዚሁ ሰዓት ይታሸጋል፡፡
  7. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቋራ/ወ/ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 በቀን 13/12/2017 ዓ/ም 4፡00 ይከፈታል፡፡
  8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ ስማቸውንና ፊርማቸው የድርጅቱን ማህተም ማስቀመጥ ይኖርባችኋል፡፡
  10. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥና ንብረት አስ/ቡድን ወይም ቋራ ወረዳ ገን/ጽ/ቤት በስልክ ቁጥር 058 271 00 31 /02 69 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡- የመክፈቻ ቀን ሎት 1 መኪና መለዋወጫ እቃዎችን በ13/12/2017 ዓ/ም 3:30 ታሽጎ 4:00 ይከፈታል ፤ሎት 2 የመኪና ጎማ በ13/12/2017 9:30 ታሽጎ 10:00 ይከፈታል አሸናፊው ድርጅት የመኪና ጎማውን  የቋ/ወ/ገን/ጽ/ቤት ድረስ ማምጣት አለበት፡፡

የቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here