ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
43

በአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት የተለያዩ እቃዎችን ማለትም ሎት 1 ያገለገሉ አሮጌ ተመላሽ ጎማ እና ሎት 2 ያገለገሉ አሮጌ ተመላሽ የመኪና ባትሪ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

  1. በጨረታው ማናኛውም ተጫራች መሣተፍ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  2. ተጫራቾች የንብረቶችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ በጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ ቢሮ ቁጥር 19 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም (ቢድ ቦንድ) ጠቅላላ ዋጋ 5 በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመ/ቤቱ ሥም ደረሰኝ በማስቆረጥ ጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ማስያዝ አለባቸው፡፡
  5. ለሽያጭ የቀረቡ ንብረቶችን ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች በጎጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት ድረስ በመቅረብ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 11፡30 ድረስ ማየት ይችላሉ፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን (መጫረቻውን) ዋናውን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢሮ ቁጥር 19 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ በሥራ ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ እስከ 6፡30 ከነሐሴ 12/2017 ዓ/ም እስከ መስከረም 2/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
  7. ጨረታው በ16ኛው ቀን መስከረም 2/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 19 ይከፈታል፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ የሚለየው በየሎቱ ባለው ጠቅላላ ዋጋ ይሆናል፡፡
  9. ተጫራቾች ሊሸጥ ከተዘጋጀው የንብረት ወይም የዕቃ ዓይነት ከተገለጸው መጠን (ብዛት) ቀንሰው መወዳደር አይችሉም ፤ሁሉንም ንብረቶች ማንሳት አለባቸው፡፡
  10. ተጫራቾች በመወዳደሪያ ፖስታቸው ላይ ሥም፣ ፊርማ ሥልክ ቁጥራቸውን  መጻፍ አለባቸው፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 771 18 18 በመደወል እና መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የጐጃም ገጠር መንገድ ጥገና ጽ/ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here