ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
114

የፍኖተ ሰላም ከተማ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለመ/ቤቱ አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ ዕቃዎች ማለትም ሎት 1 -75 ኪሎ ዋት ሠርፈስ  የዉሃ ፓምፖች እና ሎት 2 ኤክስትራክተር በግልጽ  ጨረታ የግዥ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩ መስፈርቶችን የሚያሟሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
  3. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  4. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
  5. የግዥዉ መጠን ከብር  200‚000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ተጨማሪ  እሴት ታክስ (ቫት) የተመዘገቡ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  6. የተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ብር አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም በዉሃ አገልግሎቱ  ደረሰኝ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  7. ተጫራቾች ከ1-6 የተዘረዘሩትን ማሰረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
  8. የጨረታ ማስታወቂያዉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ይቆያል፤ በ15ኛዉ ቀን 11፡30 ሳጥኑ ይታሸጋል ፤በ16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 3፡30  ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ  ቢገኙም ባይገኙም  በግልጽ ይከፈታል፡፡
  9. ማንኛዉም ተጫራች ሀሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ ቢሮ ቁጥር አራት  በተዘጋጀዉ  የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. በተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማስገባት አይቻልም፡፡
  11. የጨረታ መክፈቻዉ ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለዉ  የሥራ ቀን  በተመሳሳይ  ሰዓት ይከፈታል፡፡
  12. በጨረታዉ ለተሸነፉ ተጫራቾች ከአሸናፊዉ ጋር ዉል እንደተያዘ የጨረታ ማስከበሪያዉ ይመለሳል፡፡
  13. ተጫራቾች የማይመለስ ለእያንዳንዳቸው ብር 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 2 ዘወትር በሥራ ሰዓት መዉሰድ ይችላሉ፡፡
  14. አሸናፊዉ ተጫራች ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት  ዉስጥ ያሸነፉበትን የሎት ዕቃዎች ጠ/ዋጋ የዉል ማስከበሪያ ዋስትና የሚሆን 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) /በጥሬ ገንዘብ ለፍኖተ ሰላም ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት አስይዘዉ ዉል በመፈጸም ያሸነፉትን ዕቃ ፍኖተ ሠላም ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸዉ፡፡
  15. ተመሳሳይ የሆኑ እቃዎች በአንድ ምድብ (ሎት) በማድረግ ዉድድሩ የሚገለጸዉ በጠቅላላ የድምር ዉጤት ነዉ፡፡
  16. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ (በከፊል) የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  17. በጨረታዉ መሰረዝ ምክንያት ተጫራቾች ላወጡት ወጪ መ/ቤቱ ኃላፊነትን አይወስድም፡፡

ለበለጠ መረጃ  በስልክ ቁጥር 058 775 13 87 /00 75/ 09 23 4 26 123 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የፍኖተ ሠላም ከተማ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here