ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
16

የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ በደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር መኪና ላላቸው ተቋማት የተለያዩ የሞተር ዘይቶች እና ቅባቶች በግልጽ ጨረታ  አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፉ በተጠቀሰው የጨረታ ዓይነት በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. ያቀረቡት ዋጋ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ (ቫት) ተመዝጋቢ መሆናቸውንን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የተዘረዘሩትን መረጃዎች ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙ ማቴሪያሎችን ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የዋስትና (ቢድ ቦንድ) ሚወዳደረበት የዕቃዎችን ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም ደብር ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን አንድ ኮፒ እና ኦርጅናል ሥርዝ ድልዝ በሌለበት የተጫራቾችን ሥም ፊርማ፣ ማህተም ጨረታው ያወጣው መ/ቤት ስምና አድራሻ በመግለፅ በደ/ታ/ከ/አስ/ገንዘብ መምሪያ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታው በጋዜጣ ከመጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ቀን ድረስ ባሉት ቀናት ማስገዛት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታው ግዥ ንብ/ድን በ16ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡10 ይከፈታል፡፡
  9. ጨረታው የሚከፈትብት እለት በዓል ቀን ከሆነ የሚታሸገውና የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ሰዓቱን ጠብቆ ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመሰስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  11. ተጫራቾች በዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ በተመለከተው መሰረት የእያንዳንዱን ዋጋና ጠቅላላ ዋጋ መግለፅ አለባቸው፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራች ከነጠላ ዋጋ ሆነ ከጠቅላላ ዋጋ ላይ በተጫራቾች የሚሞላ ሰነድ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለው ፓራፍ ቢሆንም ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  13. በማንኛውም ሁኔታ ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መጫረት አይችሉም፡፡
  14. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  15. ውድድሩ በሎት ስለሆነ አንድም እቃ ሳይሟላ መቅረብ የለበትም ሳይሞላ ከተገኘ ከውድድሩ ውጭ ይሆናሉ፡፡
  16. የእቃው መጠን አስከ 20 በመቶ ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል፡፡
  17. መምሪያው በጨረታ ሰነድ ላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ የመረጠውን ዓይነት የመግዛት መብት አለው፡፡
  18. እቃው የሚቀርብበት ቦታ ደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ ድረስ ይሆናል፡፡
  19. ጨረታው ሲከፈት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል፡፡
  20. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ማሣሠቢያ፡- ስለጨረታው ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ ደ/ከ/አስ/ገን/መምሪያ ግዥ ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ወይም በሥልክ ቁጥር 058 441 02 09 /058 141 93 75 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here