ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
114

የቻግኒ ከ/አስ/ጤ/አጠ/ጣቢያ ለ2017 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል መድሃኒት እና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሠረት መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሠ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ቲን/ ያላቸው፡፡ ከ200,000.00 /ከሁለት መቶ ሺ ብር/ በላይ ለሆነ ግዥ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ ሰነዶችን ኮፒ ተደርገው ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር ማያያዝ የሚችሉ፡፡
  2. የሚገዙ መድሃኒት እና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡ የጨረታ ሰነዱ የሚሸጥበት ቦታ ቻ/ከ/አስ/ጤ/አጠ/ጣቢያ ግዥ እና ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 5 ነው፡፡
  3. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት መድሃኒት እና የህክምና መገልገያ መሣሪያዎች ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ጤ/ጣቢያ ግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን በ16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ ጨርሰው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. የጨረታ ማስታወቂያው በ16ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ተወዳዳሪዎች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውን ቢገኙም ባይገኙም በግልጽ ይከፈታል፡፡
  6. አሸናፊ ድርጅት እቃዎችን ጤና ጣቢያ የንብረት መጋዝን ድረስ በማቅረብ ጥራታቸውን ታይቶ በዝርዝር ማስረከብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
  7. አሸናፊ ድርጅት የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በማስያዝ ውል መውሰድ የሚችል መሆን አለበት፡፡
  8. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  9. የጨረታ ሰነዱን 200.00 /ሁት መቶ ብር/ በመግዛት መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የቻግኒ ከ/አስ/ጤ/አጠ/ጣቢያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here