ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
38

በአብክመ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት በግቢዉ ዉስጥ የተጠራቀሙ የተለያዩ ቁርጥራጭ ብረቶችን እና የተለያዩ የተሸከርካሪ ባትሪና ጎማወችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. የሚሸጡ እቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ናሙና የቀረበ ስለሆነ የጨረታ ሰነዱን ሲወስዱ በማየት ማግኘት ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታ መስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) 100,000,00 /አንድ መቶ ሽህ/ ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው::
  3. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ/ንብ/አስ/ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ከ 26/01/2018 ዓም እስከ 11/02/2018 ዓም ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
  4. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ / ብር በመክፈል ከገንዘብ ያዥ ቢሮ መዉሰድ ይችላሉ፡፡
  5.  ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛዉ ቀን በግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን በ11/02/2018 ዓም በ4፡00 ታሽጎ በ4፡30  ይከፈታል ሆኖም ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታዉን ለመክፈት እንገደዳለን ፡፡
  6. አሸናፊዉ የሚለየዉ በእያንዳንዱ እቃ  ከፍተኛ ዋጋ ባቀረበ ይሆናል፡፡
  7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  8. ተጫራቾች ያሸነፉትን እቃዎች  በባ/ዳር ከ/አስ/መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት ግቢ በመገኘት መረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  9. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በባ/ዳር ከ/አስ/መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ንብረት አስ/ቡድን ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 320 18 78 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡

የባህርዳር ከ/አስ/ መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here