ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
37

በሰሜን ጎንደር ዞን የጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ በጀት በሥሩ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት1.የመኪና መለዋወጫ እቃዎች ፣ ሎት 2. የመኪና ጎማና ባትሪ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፤ ስለሆነም ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፤ ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፡-

  1. በዘመኑ በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ  ኮፒ ማቅረብ  ይጠበቅባቸዋል፡፡
  2. የቲን ነምበር ተመዝጋቢ የሆኑ እና ኮፒ ማቅረብ  ይጠበቅባቸዋል፡፡
  3. ለተጨማሪ ሴት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢዎች የተጨማሪ ሴት ታክስ ማረጋገጫቸውን ሰርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የዕቃዎቹን አይነትና ዝርዝር መገለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት  ቢሮ ቁጥር 07 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 1.5 በመቶ ከሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አስበው በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና ማለትም በአማረኛ የተተረጎመ ወይም በመ/ቤቱ ገንዘብ ያዥ በመ/ሂ-1 አንድ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከመስከረም 26 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ይውላል፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢሮ ቁጥር 10 ጃ/ወ/ገ/ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ቀናት ከመስከረም 26 ቀን 2018 እስከ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጃ/ወ/ግ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 10 በቀን ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ/ም 8፡00 ታሽጎ 8፡15 ይከፈታል፤ ሆኖም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኝም ባይገኙም የጨረታ ከፈታ ስርዓቱን አይስተጓጎልም፡፡
  11. ጨረታውን የምናወዳድረው በጠቅላላ ድምር ሲሆን ጨረታው ለ30 ተከታታይ ቀናት ፅንቶ ይቆያል፡፡
  12. ተጫራቾች ከጨረታው ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ ሊኖረው አይፈቀድም ካለውም ፓራፍ ይደረግበት፡፡
  13. ተጫራቾች ከሚሞሉት ሰነድና ፖስታ ላይ የድርጅታቸውን ህጋዊ ማህተም ማድረግ አለባቸው፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. ተጫራቾች የእቃዎቹን ርክክብ የሚፈጸመው ጥራታቸው በባለሙያ እየተረጋገጠ ማ/ጎንደር ዞን ከሻጭ መጋዝን ነው፡፡
  16. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 294 00 23 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ጃናሞራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here