ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
38

በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ ፍ/ቤት ግዥ ለሚፈፀማቸዉ በመደበኛ በጀት ሎት 1. የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2. ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 3 የጽዳት እቃ፣ ሎት 4 ቋሚ እቃ ሎት 5 ህትመት እንዲሁም ሎት 6 የችሎት ካባ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ማሰራት ይፈልጋል፤ ስለዚህ በዘርፍ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ ማንኛዉም ተጫራች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
  3. የግዥ መጠኑ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዘጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም /ቢድ ቦንድ/ እስከ 60 /ስልሳ/ ቀን ያላነሰ የሆነ የሚወዳደሩበት የእቃው ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በጥሬ ገንዘብ /ሲፒኦ/ ማስያዝ የሚችሉ፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን አንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በለጋምቦ ወረዳ ፍ/ቤት በግዥ ቡድን ወይም በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ሁሉም ውድድሩ የሚካሄደው በሎት ወይም በነጠላ አሸናፊው ለሚሆነው ነው፡፡
  8. የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳማና እሁድ እንዲሁም በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል፡፡
  9. መ/ቤቱ በእያንዳንዱ ግዥ ላይ 20 በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. የጨረታ ሰነዱ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከጨረታ ውጭ ይሆናሉ፡፡
  11. አሸናፊው ድርጅት እቃውን የሚያስረክበው በፍ/ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ለመ/ቤቱ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡
  12. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 20 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በሥልክ ቁጥር 033 114 02 83 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. ተጫራቾች በፖስታው ላይ ቀን፣ ሥም፣ ፊርማ እና ስልክ ቁጥር የሚወዳደሩበት ዘርፍ መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡
  14. በጨረታው ለመሳተፍ ለሚፈልጉ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 20 (ሃያ ብር) በመክፈል ለጋምቦ ወረዳ ፍ/ቤት ቢሮ ቁጥር 20 በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የለጋምቦ ወረዳ ፍርድ ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here