በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የአዲስ ቅዳም ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እና ቋሚ አላቂ ዕቃ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 3 የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ሎካል ፈርኒቸር፣ ሎት 4 የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ኢምፖርትድ ፈርኒቸር እንዲሁም ሎት 5 ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ እያንዳንዱን ሎት በሎት ድምር አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፤ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳዳር ትችላላቸችሁ፡፡
- የዘመኑ የታደሠ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው የአገልግሎቱ መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታከስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ከላይ ከ1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎችን ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሠነድ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን እያንዳንዱን ሎት በማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል አዲስ ቅዳም ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ወይም የዕቃውን አገልግሎቱን ጠቅላላ ዋጋ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እና ቋሚ አላቂ ዕቃ ብር 5,000 ፤ሎት 2 የጽዳት እቃዎች ብር 1,000 ፤ ሎት 3 የቤትና የቢሮ ዕቃዎች ሎካል ፈርኒቸር ብር 10,000 ፣ሎት 4 የቤትና የቢሮ ዕቃዋች ኢምፖርትድ ፈርኒቸር ብር 5,000 እንዲሁም ሎት 5 ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ብር 10,000 በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ አዲስ ቅዳም ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት ህጋዊ ደረሰኝ መሂ-1 ተቆርጦ ኮፒውን ከሠነዱ ጋር ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥና ፋይ /ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 3 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ 16ኛው ቀን 4፡00 ድረስ በሳጥኑ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- እንደ በጀቱ አቅም 20 በመቶ የመጨመር እና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በያንዳንዱ ምድብ አሸናፊ የሚሆነው ድርጅት መስፈርቱን በሟሟላት ከያንዳንዱ በሎት ድምር ዝቅጸተኛ ዋጋ የሞላው ነው፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በ16ኛው ቀን 4፡00 ተዘግቶ 4፡30 ይከፈታል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በዚሁ ሠዓት ተዘግቶ በዚሁ ሠዓት ይከፈታል፡
- አሸናፊ ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 ሥራ ቀናት በኋላ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ አዲስ ቅዳም ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት በማስያዝ ውሉን መፈጸም ይኖርበታል፤ በተባለው ቀን መጥቶ ውሉን የማይፈጽም ከሆነ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
- አሸናፊው ውል ከፈጸመ በኋላ የአሸነፋቸውን ዕቃዎች አዲስ ቅዳም ከተማ ድረስ አጓጉዞ ያደርሳል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአካል ወይም በስልክ ቁጥር 058 450 06 54 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የአዲስ ቅዳም ከተማ አስ/ገ/ጽ/ቤት