ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
34

በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለተሁለደሬ ወረዳ ውሃና ኢ/ል ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውሉ በመደበኛ በጀት ሎት 1 የህንፃ መሳሪያ፣ ለተሁለደሬ ወረዳ ጤና ጥ/ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል በUNDP በጀት ሎት 2 የሀክምና መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. ህጋዊና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ
  4. ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተዘረዘሩት ማስረጃዎች ጎላ ብለዉ መነበብ መቻል አለባቸው፡፡
  5. ጨረታ ሰነዱን ሲገዙ ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ከተሁለደሬ ወረዳ ገ/ኢ/ትብብር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 7 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለህንፃ መሳሪያ፡ ብር 10,000 /አስር ሽህ ብር/ ለህክምና መሳሪያዎች ብር 20,000 /ሀያ ሽህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
  7. የጨረታ ሰነዱን ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሽገ ፖስታ ተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 10 ከጥቅምት 12/2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 02/2018 ዓ.ም 4፡00 ድረስ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታዉ በህዳር 02/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል፡፡ (ባይገኙም ይከፈታል) የጨረታ መክፈቻ ጊዜዉ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
  9. የጨረታ መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው በቀጣይ የሥራ ቀን የመክፈቻ ሰዓቱን ጠብቆ ይከፈታል፡፡
  10. አሸናፊው የሚለየዉ በሎት /በድምር/ ዋጋ ነዉ፡፡ በሰነዱ የተዘረዘሩትን እቃዎች ዋጋ በሙሉ ያልሞላ ተጫራች ከጨረታዉ ዉጭ ይሆናል፡፡ አሸናፊ ሆኖ የተመረጠዉ ተጫራች መ/ቤቱ በጠየቀዉ (ስፔስፊኬሽን) መሰረት የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
  11. ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር የተጋነነ ሆኖ ከተገኘ ጨረታዉ ዉድቅ ይሆናል፡፡
  12. ሁሉም የሚቀርቡ እቃዎች ጥራታቸዉን የጠበቁ መሆን አለባቸዉ፡፡ አሸናፊዉ ድርጅት እቃዎቹን ተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ በራሱ ወጭ አጓጉዞ በማቅረብ ንብረቱን በየንብረት ክፍሉ አስረክቦ ገንዘቡን ወጭ አድርጎ ይወስዳል፡
  13. ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለዉጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታዉ ራሳቸዉን ማግለል አይችሉም፡፡
  14. ጨረታዉን ለማዛባት የሞከረ ተጫራች ከጨረታዉ ዉጭ ሆኖ ወደፊትም በመንግስት ጨረታዎች አንዳይሳተፍ ይደረጋል፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  16. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 033 222 00 12 ደውለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here