በደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር የኮምቦልቻ እንስሳት በሽታ ቅኝት ጥናት ምርመራ ላብራቶሪ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የሥራ ሂደት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚዉሉ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃ፣ ሎት 3 የመኪና እቃ የመደበኛ፣ ሎት 4 የመኪና እቃ የፕሮጀክት፣ ሎት 5 የመኪና እቃ ጥገና የመደበኛ እና ሎት 6 የመኪና እቃ ጥገና የፕሮጀክት ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሠ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
- የቫት እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- በአዲሱ የንግድ ፈቃድ መሠረት ንግድ ፈቃድ ያወጡ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ተመዝጋቢነት ሠርተፊኬት ያላቸዉ፡፡
- ለመኪና ጥገና ተጫራቾች ደረጃ 2፣3 እና በላይ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-6 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዳቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
- የሚገዙ እቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሠነዱ ጋር ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛዉ ቀን ድረስ ሠነዱን የማይመለስ ለአንድ ሎት ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል በኮ/እ/በ/ቅ/ጥ/ም/ላብራቶሪ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የዕቃ አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ አሸናፊ ከሆኑ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ እና ለመኪና ጥገና 3 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማሲያዝ አለባቸዉ፡፡
- ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅች ማለትም ዋናና ኮፒ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ለኮ/እ/በ/ቅ/ጥ/ም/ላብራቶሪ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታዉ ተጫራቾች ባሉበት ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በኮ/እ/በ/ቅ/ጥ/ም/ላብራቶሪ ግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 2 ከጥቅምት 24/2018 – ህዳር 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ተቆጥሮ በ16ኛዉ ቀን 4፡00 ተዘግቶ በዚያዉ ቀን 4፡30 ላይ የሚከፈት ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም በካላንደር ዝግ ከሆነ በሚቀጥለዉ ቀን በዚያዉ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ለመኪና ጥገና አሸናፊ የሚሆነው ተጫራች ለአንድ አመት ውል ገብቶ መስራት የሚችል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- ስለጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 1 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 033 351 88 43 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኮምቦልቻ እንስሳት በሽታ ቅኝት ጥናት ምርመራ ላብራቶሪ

