ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
55

በደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ በደ/ታቦር ከተማ አስተዳደር ላሉ ተቋማት የጽህፈት መሳሪያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ተጫራች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፉ በተጠቀሰው የጨረታ ዓይነት በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. ያቀረበው ዋጋ ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የተዘረዘሩትን መረጃዎች ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙ ማቴሪያሎችን ዝርዝር መግለጫ (ሰፔስፊሌሽን) ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የዋስትና (ቢድ ቦንድ) በሚወዳደሩበት የዕቃዎች ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም ደብር ታቦር ከተማ አስ/ገን መምሪያ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን አንድ ኮፒ እና ኦርጅናል ሥርዝ ድልዝ በሌለበት የተጫራቾችን ሥም፣ ፊርማና ማህተም ጨረታውን ያወጣው መ/ቤት ስምና አድራሻ በመግለጽ በደ/ታ/ከ/አስ/ገንዘብ መምሪያ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ቀን ድረስ ባሉት ቀናት ማስገባት ይኖርባቸል፡፡
  8. ጨረታው ግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን በ16ኛው ቀን 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡10 ይከፈታል፡፡
  9. ጨረታው የሚከፈትብት እለት በዓል ቀን ከሆነ የሚታሸገውና የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ሰዓቱን ጠብቆ ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  11. ተጫራቾች በዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ በተመለከተው መሰረት የእያንዳንዱን ዋጋና ጠቅላላ ዋጋ መግለጽ አለባቸው፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራች ከነጠላም ዋጋ ሆነ ጠቅላላ ዋጋ ላይ በተጫራቾች ላይ የሚሞላ ሰነድ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለው ፓራፍ ቢሆንም ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  13. በማንኛውም ሁኔታ ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ (ተመስርቶ) መጫረት አይችልም፡፡
  14. የጨረታ መዝገጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  15. ውድድሩ በሎት ስለሆነ አንደም እቃ ሳይሟላ መቅረብ የለበትም ሳያሟላ ከተገኘ ከውድድሩ ውጭ ይሆናል፡፡
  16. የእቃው መጠን እስከ 20 በመቶ ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል፡፡
  17. መምሪያው በጨረታ ሰነድ ላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ የመረጠውን ዓይንት የመግዛት መብት አለው፡፡
  18. እቃው የሚቀርብበት ቦታ ደብረታቦር ከተማ ገንዘብ መምሪያ ድረስ ይሆናል፡፡
  19. ጨረታው ሲከፈት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡
  20. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስለጨረታው ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ ደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደር ገንዘብ መምሪያ/ግዥ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ወይም በስልክ ቁጥር 058 441 02 09 /058 141 93 75 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደብረ ታቦር ከተማ አስስተዳደር ገንዘብ መምሪያ

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here