የቡሬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግቢው ውስጥ የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለህጋዊ ነጋዴዎች መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው እና ጠቅላላ ዋጋው ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የጨረታ መቆያ ጊዜ ከህዳር 1/2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 15/2018 ዓ.ም ለ15 ተከታታይ ቀናት ብቻ ሲሆን ተጫራቾች ሰነዱን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከህዳር 1/2018 ዓ.ም አስከ ህዳር 15/2018 ዓ.ም እስከ 11፡30 የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተወዳዳሪዎች ብር 20,000 /ሀያ ሽህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ጨረታው የሚዘጋበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን በ16ኛው ቀን ህዳር 16/2018 አ.ም ጠዋት 3፡30 የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በተመሳሳይ ቀን 3፡45 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ለመክፈት አይስተጓጎልም፡፡
- የመክፈቻ ቀኑ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው በሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ማሸነፋ በተገለጸ ከአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት በኃላ ባሉት አምስት የሥራ ቀናት ውሥጥ ውል መያዝ አለበት፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር 058 774 07 71 ደውሎ ወይም በአካል ቀርቦ መረዳት ይችላሉ፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
- ሌሎች በዚህ የጨረታ ማስታወቂያ ያልተካተቱ ጉዳዩች ካሉ በግዥ መመሪያ የምንገዛ ይሆናል፡፡
- የማስመዘኛና የማስጫኛ ወጭዎች በአሸናፊ ድርጅቶች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
ቡሬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

