የእብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለእብናት ወረዳ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1. የጽ/መሳሪያ፣ ሎት 2 ኤሌክትሮኒክስ እቃ ሎት 3 የጽዳት እቃ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ሁሉ መወዳደር የምትችሉ ትችላላችሁ፣
- የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ (የቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጠቅላላ ዋጋ ድምር አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዛዝ (ሲፒኦ) በእብናት ወረዳ ገንዘብ/ጽ/ቤት ስም በማሰራት ወይም በጥሬ ገንዘብ እብናት ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ዋና ገ/ያዥ ገቢ በማድረግ ግቢ የሆነበትን የገቢ ደረሰኝ ከኦርጅናል የጨረታ ሰነዱ ጋር ታሽጎ መቅረብ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን ሰነድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ውስጥ አድርጎ ኦርጅናል ሰነድ እብናት ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 06 ባዘጋጀዉ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታዉ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለተከታታይ ለ15 ቀን ይቆያል፡፡ በ16ኛው ቀን ይከፈታል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች (ህጋዊ ወኪሎቻቸው) ቢገኙም ባይገኙም በግዥና ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 06 ጨረታው በወጣ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ላይ ይከፈታል፡፡ ቀኑ በአል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ለስራ በተፈለገበት ስዓት ለ3 ቀናት ተጠብቆ ካልቀረበ በመመሪያ መሰረት መ/ቤቱ እርምጃ ለመውሰድ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ዝርዝር በሚሞሉበት ሰዓት ሥርዝ ድልዝ ወይም በፍሉድ የጠፋ መሆን የለበትም ሥርዝ ድልዝ ያለው ከሆነም ፓራፍ መደረግ አለበት፡፡
- ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዱ ዉስጥ አንዱን ያልሞላ ከጨረታ ወጭ ይሆናል፡፡
- አሸናፊ የሚለየዉ በጥቅል ድምር ይሆናል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 08 የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ደረቅ ቸክ ማስያዝ አይቻልም፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱን እንደተገለፀለት ከ5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ በመቅረብ የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መውሰድ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡
- ጨረታዉ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ 20 ቀን ይሆናል፡፡
- አሸናፊዉ ድርጅት በወጣዉ ጨረታ መሰረት ከሚያቀርባቸዉ ዕቃዎች ውስጥ ተቋሙ በሚፈልገው ልክ ናሙና ለሚያስፈልጋቸዉ እቃዎች ናሙና ማቅረብ እና በአቀረባቸዉ ናሙና መሰረት ማቅረብ የሚችል፡፡
- አሸናፊዉ ድርጅት እታዉን የሚያቀርበዉ እብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 06 በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 058 440 06 06 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የእብናት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

