ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
105

በደቡብ ጎንደር አስተዳዳር ዞን የፋርጣ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ዋ/ጽ/ቤት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች በመደበኛ በጀት ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የስፖርት ትጥቅ፣ ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ፣ ሎት 4 አርኒቸር እና ሎት 5 የመኪና ጐማ በግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ  አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች፡-

በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡

የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡

ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ክፒ ከመጫሪቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡

ይህ ግልጽ ጨረታ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ድረስ በፋርጣ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ዋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 በመምጣት ከዋናው ጋር ሊገናዘብ የሚችልና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማስረጃ በማቅረብ  እያንዳንዱን ሰነድ የማይመለስ 30.00 /ሰላሳ ብር/ በመክፈል ማግኘት ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር በሞሉት ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /በጥሬ ገንዘብ/ ማስያዝ አለባቸው፡፡

ተጫራቾች በባንክ ያስያዙትን ገንዘብ /ሲፒኦ/ ወይም  /ጥሬ ገንዘብ/ ከመ/ቤታችን ገቢ ያደረጉበትን የገቢ ደረሰኝ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ፖስታ አሽገው ፋ/ወ/ገ/ኢ/ል/ዋ/ጽ/ቤት ብለው በዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ቢሮ ቁጥር  5 እስከ 16ኛው ከቀኑ 3፡30  ድረስ ማስገባት የሚቻል ሲሆን የሚታሸገውም በዚሁ ሰዓት ነው፡፡

ጨረታው ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት /ባይገኙም/ በግዥና  ንብረት አስተዳደር ቡድን  ቢሮ ቁጥር 5 በ 16ኛው ቀን በ 3፡45 ይከፈታል፡፡

የጨረታ መከፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡

የጨረታ አሸናፊው የሚሆነው በጥቅል /በሎት/ ነው፡፡

የሚገዙ  ዕቃዎች ርክክቡ የሚፈፀመው በሙያተኛ ተረጋግጦ ነው፡፡

አቅርቦቱ ደቡብ ጎንደር ዞን ደ/ታቦር ከተማ ፋርጣ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 ይሆናል፡፡፡

የሚገዙትን ዕቃዎች ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡

መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስለ ጨረታው ዝርዝር መግለጫ በስልክ ቁጥር 058 441 30 36 መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የፋርጣ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ዋ/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here