በሰሜን ጎጃም ዞን የይልማና ዴንሳ ወረዳ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ለይልማና ዴንሳ ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚዉሉ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና የይ/ደወ/ትምህርት ጽ/ቤት የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ማለትም ሎት 1 ኮቲ ቀበሌ፣ ሎት 2 አንጋር፣ ሎት 3 ትሎማ እና ሎት 4 አይባር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት እና ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛዉም ተጫራች መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- የቲን ተመዝጋቢ መሆናቸዉን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በዘርፉ አግባብነት ያለዉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የኤሌክትሮኒክስ ግዥው ከብር 200‚000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ (የቫት) ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው ለግንባታዎች ከደረጃ 10 እና በላይ ያሉ የህንጻ ተቋራጮችን መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ሂሳብ ኤሌክትሮኒክስ 30,000 /ሰላሳ ሽህ ብር/ እና የግንባታዎች 32,500/ ሰላሳ ሁለት ሽህ አምስት መቶ ብር/ ብቻ በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ከዋና ገንዘብ ያዥ አስይዘዉ ለግዥ ኦፊሰሮች ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል ወይም በባንክ የተረጋገጠ (ሲፒኦ) ከሆነ ከፖስታ ዉስጥ አስገብተዉ ማሸግ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ካለ ከአሸናፊዉ ዋጋ ጋር ተደምሮ ሲያዝ የተሸነፈዉ ተጫራች የሚያስይዘዉ ገንዘብ ይመለስላቸዋል፡፡
- ጨረታዉ የሚከፈትበት ዕለት በበዓል ቀናት ከሆነ ወደ ቀጣዩ የሥራ ቀን ይሸጋገራል፡፡
- የኤሌክትሮኒክስ ጨረታ ሰነዱን ከህዳር 15/2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 29/2018 ዓ.ም ለ15 ተከታታይ ቀናት እና የግንባታዎች ጨረታ ሰነዱን ከህዳር 15/2018 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 05/2018 ለ21 ተከታታይ ቀናት በጋዜጣ ወጥቶ የሚቆይ ሲሆን የተሞላበትን ፎርም ቲን፣ የንግድ ፈቃድዎንና ሌሎች ያልተጠቀሱ ማስረጃዎችን በታሸገ ፖስታ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የኤሌክትሮኒክስ ጨረታዉ የሚዘጋበት ህዳር 30/2018 ዓ.ም በ3፡30 ሲሆን ጨረታዉ የሚከፈተዉ በዚሁ ቀን ህዳር 30/2018 ዓ.ም በ4፡00 ቢሮ ቁጥር 3 ፍላጎት ያላቸዉ ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ እንዲሁም የግንባታዎች ጨረታዉ የሚዘጋበት ታህሳስ 06/2018 ዓ.ም በ3፡30 ሲሆን ጨረታዉ የሚከፈተዉ በዚያው ቀን ታህሳስ 06/2018 ዓ.ም በ4፡00 ቢሮ ቁጥር 3 ፍላጎት ያላቸዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በጨረታዉ መክፈቻ ዕለት ባይገኙ መ/ቤቱ ጨረታዉን ለመክፈት የሚገድበዉ የለም፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ 10 በመቶ የዉል ማስከበሪያ በማስያዝ ዉል መያዝ አለበት፡፡
- ተጫራቾች አሸገዉ ከሚያስገቡት ሰነድ እና ፖስታ ላይ አድራሻና የድርጅቱ ማህተም መኖር አለበት፡፡
- ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
- ጨረታዉን የምናወዳድረዉ በሎት (በጠቅላላ) ዋጋ ነዉ፡፡
- ግዥ ፈጻሚ አካል ያሸነፈውን ተጫራች በሚመርጥበት ጊዜ እንዳስፈላጊነቱ 20 በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- የሚሞላው ዋጋ ማንኛውንም ታክስ ያካተተ መሆን አለበት፡፡
- ጨረታዉ ለ40 ቀናት ጸንቶ ይቆያል፡፡
- የኤሌክትሮኒክስ ጨረታ ሰነዱ የሚሸጥበት ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ ነዉ፡፡
- የግንባታ ጨረታ ሰነዱ የሚሸጥበት ብር 400 /አራት መቶ ብር/ ብቻ ነዉ፡፡
- በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች ተጨማሪ ማስረጃ ቢያስፈልጋቸዉ የይ/ዴ/ወ/ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 3 ወይም በስልክ ቁጥር 0583380298 ማግኘት ይችላሉ፡፡
የይልማና ዴንሳ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብ ጽ/ቤት

