ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
88

በአብክመ ዋና ኦዲተር ደሴ ወኪል መ/ቤት ሎት 1. የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2. የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 3. የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ሎት 4. የፈርኒቸር እቃዎች እና ሎት 5. የህንፃ መሳሪያ ዕቃዎች ህጋዊ ተጫራቾችን በማወዳደር ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-

  1. ማንኛዉም ተጫራች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ ከመንግስት የሚጠበቅባቸዉን የዘመኑን ግብር የከፈሉና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተቀበሉ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት የሚያቀርቡ፡፡
  2. ለዚህ የተዘጋጀውን ሠነድ ቢሮ ቁጥር 05 በአካል በመቅረብ በብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. የጨረታው ሠነድ ያለምንም ሥርዝ ድልዝ መሞላት ይኖርበታል፡፡
  4. የተሞላው ዋጋ ቫትን የሚጨምር ወይም የማይጨምር መሆኑ መግለጽ ይኖርበታል፡፡ የተገለፀ ነገር ከሌለው (ከቫት) ጋር እንደተሞላ ይቆጠራል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ አንድ በመቶ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዛቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ከሠነድ ጋር አብሮ አያይዞ መቅረብ አለበት፡፡
  6. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ወጥቶ የሚቆይ ሆኖ በ16ተኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጐ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚሁ ቀን በ4፡00 ይከፈታል፡፡
  7. መ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. ለበለጠ መረጃ በአካል ቢሮ ቁጥር 05 በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 033 312 00 63 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የአብክመ ዋና ኦዲተር ደሴ ወኪል መ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here