የእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 በጀት አመት ሁለተኛ ዙር የወጣ ለጥገና አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የህንጻ መሳሪያ፣ ሎት 2 ብረታ ብረት፣ ሎት 3 ኤሌክትሪክ፣ ሎት 4 ኤሌክትሮኒክስ እቃ፣ ሎት 5 ኤምዲኤፍ እና የኮርኔስ ፕላስቲክ፣ ሎት 6 አውቶ፣ ሎት 7 ጽዳት እቃ ፣ ሎት 8 ቴክስታይል ጋርመንት ፣ ሎት 9 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 10 አገልግሎት ግዥ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ (ጥገና) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ፡- ተጫራቾች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ግዴታዎች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋዮች መለያ ቁጥር (ቲን) የተሰጣቸው እና ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የሚገዙት ዕቃዎች በተጠየቀው ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኪሽን) መሰረት ሆኖ የጨረታ ሰነዱን እንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ማግኝት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የግዥውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በመሂ 1 ወይም በባንክ ከተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሃሳብ ማቅረቢያ ቅጹን በጥንቃቄ በመሙላት በታሸና ፖስታ ከግዥ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 7 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስታወቂያዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11፡30 ድረስ ሰነዱን በመግዛት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 7 በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ባይገኙም በተደረገው የጨረታ አከፋፈት ሥርዓት ተገዥ ይሆናሉ፡፡
- ኮሌጁ በጨረታው አሸናፊ ላይ 20 በመቶ የመቀነስ ወይም የመጨመር መብት አለው፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ለውል ማስከበሪያ 10 በመቶ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
- የእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን የጨረታው አሸናፊ የሚለየው በሎት (በጥቅል) ወይም እንዳስፈላጊነቱ በተናጠል ዋጋ የሚለይ ይሆናል፡፡
- አሸናፊዉ ድርጅት ያሸነፈውን እቃ በሙሉ በራሱ ወጭ ኮሌጁ ግቢ ድረስ አምጥቶ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 7 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 227 02 00 በመደወል መረጃ ማግኝት ይችላሉ፡፡
የእንጅባራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

