በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 ኤሌክትሮኒክስ ዕቃ፣ ሎት 2 ቋሚ እቃ ጀነሬተር፣ ሎት 3 የመኪና ጎማ ከነካላማዳሪው፣ ሎት 4 የጽዳት እቃ እንዲሁም ሎት 5 ሌሎች አላቂ እቃዎች ከመደበኛ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የውል ማስከበሪያ የዋጋውን ጠቅላላ 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተወዳዳሪዎች የንግድ ፈቃዳቸው በሚጋብዛቸው ብቻ መወዳደር አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ በድን ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ለመኪና ጎማ ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ለኤሌክትሮኒክስ ብር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ ለጀነሬተር ብር 8,000 /ስምንት ሺህ ብር/ ለሎት 4 የጽዳት እቃ ብር 2,000 /ሁለት ሺህ ብር/ ለሎት 6 ሌሎች አላቂዎች ብር 2,000 /ሁለት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ደረሰኝ በመሂ 1 ኮፒ ማስያዝ አለባቸው፡፡ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አይቻልም፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ፖስታ በጥንቃቄ በመሙላት በታሸገ ፖስታ በባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 16 ተኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 1 ጨረታው ከወጣበት በ16 ተኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይታሸጋል፡፡ በዚህ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይከፈታል፡፡
- አሸናፊ የምንለየው ጥራቱን የጠበቀ እቃ ካቀረቡት ውስጥ በየሎቱ በጠቅላላ ድምር በዝቅተኛ ዋጋ የሞላውን ነው፡፡
- አሽናፊ ድርጅት ያሸነፏቸውን እቃዎች ባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በባለሙያ እያስፈተሽ ንብረት ክፍል ድረስ በራሱ ወጭ ገቢ ማድረግ አለበት፡፡
- ስለጨረታ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ባንጃ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ግ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 1 ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 227 06 47 /058 227 00 09/ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት እንደ ሴክተር መ/ቤቶች በጀት አቅም 20 በመቶ የመጨመር እና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታ ሳጥን የሚከፈትበት ቀን በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀናት በተመሳሳይ ቦታና ስዓት የይከፈታል፡፡
የባንጃ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

