የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የመኪና ጎማ ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳዳር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና በሙያዉ የተሰማሩ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የሚሳተፉ ተጫራቾች የእቃ (የአገልግሎቱን) ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ እቃወች (አገልግሎቶች) አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 33 የጨረታ ሰነዱን ማግኘትና ማየት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር ብቻ ) በመክፈል 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 33 ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ የሚፈልጉ ለጽ/ቤቱ ገንዘብ ያዥ በመክፈል ደረሰኙን ከዋጋ ማቅረቢያው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ግዥ አስተዳደር ዳይሬክተር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በተዘጋጀው ቀን የጨረታ ሣጥን የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ፋይ/ንብ/ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጐ በእለቱ ወይም በቀኑ 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ይሁን እንጂ
ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጽ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብት አለው። - ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 30 በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058 220 1068 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 2030 በመደወል ማግኘት ይቻላል።
የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

