ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
109

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ 1 የጽህፈት መሳሪያዎች፣ 2 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ 3 የፅዳት ዕቃዎች፣ 4 ኢምፖርትድ ፈርኒቸር፣ 5 የመኪና ጎማ ከነ ካላማዳሪው እና 6 የስፖርት እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ከአዊ ብሄ/አስ/ዞን የእን/ከ/አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት የግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 10 ዘወትር በሥራ ሰዓት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡

  1. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ጨረታው በወጣበት በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 08 ይከፈታል፡፡
  2. አሸናፊ የሚለየው በሎት ዋጋ ይሆናል፡፡
  3. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  4. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 08 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 227 12 58 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here