ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
99

የምዕራብ ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ የሠከላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግ/ን/አስ/ቡድን ለወረዳችን ሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ እቃዎችን ማለትም ሎት 1 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 2 ፈርኒቸር በግልጽ ጨረታ ድርጅቶችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታዉ ለመወዳደር የምትፈልጉ ድርጅቶች፡-

  1. በዘርፉ ህጋዊና የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ የግዥና መክፈያ መለያ ቁጥር (ቲን) እና የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግዥ መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 15 ቀናት ሰከላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 በመቅረብ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
  4. የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 20,000 (ሃያ ሽህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በጽ/ቤቱ ገንዘብ ያዥ በኩል ደረሰኝ በመቁረጥ የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ በጨረታዉ ፖስታ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  5. ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሁኖ ይቆይና በ16ኛዉ ቀን ከረፋዱ 3፡30 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በሰከላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አጥር ግቢ ዉስጥ ይከፈታል፡፡
  6. የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋበት በ16ኛዉ ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለዉ የሥራ ቀን በተባለዉ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
  7. የመጫረቻ ሰነዱ ከተጠቀሰዉ ቀንና ሰዓት ዉጭ ዘግይቶ ቢደርስ ተቀባይነት የለዉም፡፡
  8. አሸናፊ ድርጅቶች ያሸነፉበትን እቃ አይነት ከጽ/ቤቱ ንብረት ክፍል ድረስ ማንኛዉንም ትራንስፖርት፣ የማጓጓዣ እና የጫኝ አዉራጅ ወጭ ችሉ ማጓጓዝ ማስረከብ አለባቸዉ፡፡
  9. አሸናፊው የሚለየዉ በጠቅላላ ድምር ሆኖ ከተዘረዘሩት እቃዎች ከፊሉን ብቻ መሙላትና አስተካክሎ መሙላት ሥርዝ ድልዝ ማድረግ ከጨረታ ዉጭ ያስደርጋል፡፡
  10. ጽ/ቤቱ ጨረታዉን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  11. ጨረታዉ የሚዘጋጅበት ቋንቋ በአማረኛ ይሆናል፡፡
  12. ለበለጠ መረጃ ሰከላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 259 00 09 በመደወል ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የሠከላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here