በማከላዊ ጎንደር ታች አርማጭሆ ወረዳ የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2018 ዓ.ም ለመ/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ 1hz-k79 አንቡላንስ መኪና መለዋወጫ እቃ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ።
- በዘመኑ ታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ብር 100,000 (መቶ ሽህ ብር ) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ስነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ የመለዋዎጫ እቃ አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡ ጨረታው ከወጣበት ከታሕሳስ 13/2018 ዓ.ም እስከ ታሕሳስ 27/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 15 ቀናት ይቆያል፡፡
- የጨረታው ሳጥን የሚታሽገው ታሕሳስ 28/2018 ዓ/ም ከቀኑ 11፡30 ይሆናል
- ጨረታው የሚከፈተው ሁሉም ተጫራቾች ወይም ወኪላቸው ባሉበት የሳንጃ የመ/ደ/ሆስፒታል አዳራሽ በታህሳስ 29/2018 ዓ.ም ከጧዋቱ 3፡00 ይሆናል ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸዉ ባይኖሩም የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የሚወዳደሩበት አንድ በመቶ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሁለት ፖስታ ኦርጀናልና ኮፒውን ለየብቻ በመለየት በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊው ድርጀት በዓ/ህግ ጽ/ቤት ቀርቦ ውል መውሰድ ይኖርበታል።
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ ከተቀመጠው የዋጋ መሙያ ፎርም በስተቀር በማሳሰቢያ የሚሞሉ የዋጋና ሌሎች አላስፈላጊ መረጃዎችን የማንቀበል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የውል ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ በከፊል ወይም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በአል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡
- የሚያቀርቡት የመኪና መለዋወጫ እቃ ሁሉም እቃዎች ኦርጀናል መሆን አለባቸው፤ ኦርጂናል ለመሆኑ በባለሙያ (በሹፌር) እየተረጋገጠ ወደ ንብረት ክፍል ገቢ ይደረጋል፡፡
ለበለጠ መረጃ 09 18 19 85 88 / 09 39 24 50 07 መደወል ይችላሉ
የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

