ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
116

ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ዓመታዊ የቢሮ መገልገያ እቃዎችን እስቴሽነሪ፣ የኤሌክትሪክ እቃዎች ፣የኤሌክትሮኒክ እቃዎች፣የፈርኒቸር እቃዎች፣የውሃና የኮንስትራክሽን እና የሙዚቃ መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሚሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘርፉ የተሰማሩና አግባብ ያለው የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብርከፋይመለያቁጥር /ቲን/ ማስረጃ አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የተጨማሪ  እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ ከሆኑ ይህንን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ከመጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የማይመለስ  100.00 /አንድመቶብር/ ብቻ በመክፈል በሙሉዓለም ባህል ማዕከል ቢሮ ቁጥር 05 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ጨረታው በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ከቆየ በኋላ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቻው በተገኙበት 4:30 ይከፈታል፡፡ ቀጣዩ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም ሕዝባዊ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ  ከኢትዩጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ከተፈቀደላቸው በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም ከሁኔታዎች ጋር ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ጥሬ ገንዘብ ለገ/ያዥ በመክፈል የደረሰኙን ኮፒ ከመወዳደሪያ ዶክመንቱ ጋር አያይዘው ማቅረብይ ኖርባቸዋል፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች  በ2 ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ  በግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 05 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባትአለባቸው፡፡
  9. የጨረታው አሸናፊ ጨረታው በተገለጸ ከ5 ቀናት በኋላ አሸናፊው ድርጅት ላይ ቅሬታ ካልቀረበ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል መያዝ ይኖርበታል፡፡
  10.  ማንኛውም  ተጫራች ከተጠየቀው ስፔስፊኬሽን ውጭ የሚያቀርብ ከሆነ ተቀባይነት የለውም፡፡
  11.   የጨረታው አሸናፊ ተለይቶ ውል ከተያዘበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡
  12.  ተጫራቾች ሁሉንም መሞላት ያለባቸውን የጨረታ ሰነዶችን መሙላትአለባቸው፡፡ የሚመረጡት በእያንዳነዱ በየሎቱ ድምር መሰረት ዝቅተኛ ዋጋ ይመረጣል፡፡
  13.  ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ የሚሞሉት ዋጋ ቫትን ጨምሮ መሆን አለበት፡፡
  14. መስሪያቤቱ በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተጠቀሰው መጠን 20በመቶ ዝቅ ወይም ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡
  15.  ማዕከሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡እንዲሁም ተጫራቾች በጨረታ ማስታወቂያው ላይ ያልተገለጹ ሁኔታዎች ቢኖሩ በግዥ መመሪያው ተገዥ መሆን አለባቸው፡፡
  16.  ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 05 ድረስ በአካል በማግኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058-226-53-42 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
  17. ማሳሰቢያ፡-በዋጋ መሙያ ሰንጠረዡ ላይ ከተጠቀሰው ዝርዝር ስፔስፊኬሽን ውጭ መሰረዝና መደለዝ የራሱን ስፔስፊኬሽን የሞላ እና የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም እና ፊርማ ሌለበት ሰነድ የሚያቀርብ ተወዳዳሪ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡

ሙሉዓለም የባህል ማዕከል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here