የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ለ2018 በጀት አመት አገልግሎት የሚሰጡ ሎት 1 እስቴሽነሪ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃ፣ ሎት 3 ልዩ ልዩ፣ ሎት 4 ኤሌክትሮኒከስ፣ ሎት 5 ህትመት እንዲሁም ሎት 6 የመኪና ጎማ በሎት ተዘርዝሮ የቀረበ ሲሆን የተዘረዘሩትን ሎቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሰፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥ መጠኑ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ 1-4 የተጠቀሱት እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መገለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50 (ሃምሳ ብር) በመከፈል ከግዥ ከፍል ቢሮ ቁጥር 32 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የከፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና (በጥሬ ገንዘብ) ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በምዕ/ጎ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 32 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ከታህሳስ 20/2018 ዓ/ም እስከ ጥር 04/2018 ዓ/ም ድረስ ከቀኑ 11፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጥር 05/2018 ዓ.ም ከቀኑ 12፡00 የጨረታ ሳጥኑ ይታሸጋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ምዕ/ጎን/ዞን/ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ሂደት ውስጥ በግዥ ከፍል ቢሮ ቁጥር 32 ጥር 05/08 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጨረታው በግልጽ ይከፈታል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሆነው አካል ንብረቱን የሚያስረከበውና ውል የሚወስደው በምዕ/ጎ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 32 ድረስ በአካል በመገኘት በስልክ ቁጥር 058 331 07 58 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

