ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
26

በአብክመ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ስር የሰቆጣ ማረሚያ ቤት መምሪያ ለማረሚያ ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ አላቂ የጽ/መሳሪያና ፣ የመኪና መለዋወጫ እቃ፣ የስልጠና እቃ፣ የግንባታ እቃዎችን እና ቋሚ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡

  1. በዘርፉ የወጣ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  4. የግዥ መጠን ከ100,000 (ከመቶ ሺ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች በግልፅ በሚታይ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ የእቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን 50.00 (ሃምሳ ብር) በመክፈል ቢሮ ቁጥር 6 ማግኘት ይቻላሉ ፡፡
  8. የጨረታ ሰነድ የመሸጫ ጊዜ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመበት ጀምሮ ከ20/4/2018 እስከ 4/5/2018 ከጥዋቱ 3፡00 ድረስ መግዛት ይቻላል፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ አንድ ፖስታ በግዥ ኦፊሰር ቢሮ ቁጥር 6 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት በስራ ሰዓት እስከ 16ኛው ቀን ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. የጨረታ ማስከበሪያ 5,000 (አምስት ሽህ ብር) ፖስታ ውስጥ አብረው እንዲያሽጉ፡፡
  11. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ፋይ/ንብ/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 6 ፤በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ3፡00 ታሽጎ  3፡30 ይከፈታል፡፡
  12. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 6 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 14 61 23 11 እና በስልክ ቁጥር 09 92 04 68 95 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

የሰቆጣ ማረሚያ ቤት

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here