ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
82

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ውስጥ ወርክሾፕ አዳራሽ በመደበኛ ካፒታል በጀት በሙሉ ዋጋ በጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ በደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ አወዳድሮ ማስጠገን ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተለውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
  4. ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለማሸነፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ከፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚጠገኑትን ግንባታዎች የእቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ብቻ መግዛት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የጥገና ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በመ/ቤቱ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡ ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ከታህሳስ 27/2018 ዓ/ም እስከ ጥር 13/2018 ዓ/ም ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ነገር ግን ጥር 11 እና 12 ተከታታይ አመታዊ በዓል በመሆኑ ምክንያት ለ17 ቀን እንዲቆይ ሁኗል፡፡
  9. ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅ ፖስታ ማለትም ኦርጅናልና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማዕከላዊ ጎንደር ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሣጥን ዘወትር በስራ ሠዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከታህሳስ 27/2018 ዓ/ም እስከ ጥር 13/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት  ሆነ ባይገኙም ጨረታዉ በሰዓቱ በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ጥር 13/2018 ዓ/ም በ4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  12. ስለ ጨረታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በግ/ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በሞባይል ቁጥር 09 64 79 28 60 ወይም 09 18 73 44 61 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የማዕከላዊ ጎንደር ማረሚያ ቤቶች መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here