የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት ሎት1 የፅህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የፅዳት ዕቃዎች ፣ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው በሙያዉ የተሰማሩ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የሚሳተፉ ተጫራቾች የእቃውን ወይም አገልግሎቱ ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶሽህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል ፣ ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- የሚገዙ እቃዎች አገልግሎቶች አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 33 የጨረታ ሰነዱን ማግኘትና ማየት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን የማይመለስ ብር 200 ( ሁለት መቶ ብር ብቻ ) በመክፈል 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 33 ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ የሚፈልጉ ለጽ/ቤቱ ገንዘብ ያዥ በመክፈል ደረሰኙን ከዋጋ ማቅረቢያው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን የጨረታ ማስታወቂው በጋዜጣ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ፣ ፋይ/ንብ/ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የሥራ አስተዳደር ዳይሬክተር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ጨረታው በጋዜጣ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 30 በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058 220 1068 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 2030 በመደወል ማግኘት ይቻላል።
የአብከመ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት

