የቢቡኝ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በብ/የሚ/የግ/ግክ/ ቡድን በ2018 በጀት አመት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚውል የማንጎ ዘር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ እና የግብር ከፋይ መለያ (ቲን) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- የማንጎ ዘሩ 60 (ስልሳ) ኩ.ል ሁኖ በዛፉ ላይ በጣም የበሰለ ወደ ቢጫነት የተቀየረ ከበሽታና ተባይ ነጻ የሆነ፣ ያልተላጠ እና ግብዓቱ ሲቀርብ ከኳራንታይን ጥራት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸዉን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ የአሰሪው መ/ቤት እና የተጫራቹ ሙሉ ስም አድራሻ ፊርማ ማህተም በማስቀመጥ ከመጫረቻ ስነዶቻቸዉ ጋር ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለመግዛት ብር 100 (አንድ መቶ ብር) የማይመለስ በመክፈል ከቢ/ወ/ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት/ደ/ሃ/ደ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 12 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የእቃዉን ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
- ማንኛዉም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቢ/ወ/ግ/ጽ/ቤት/በብ/የሚ/የግ/ግ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 06 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ከጥር 4/2018 ዓ.ም እስከ ጥር 18/2018 ዓ.ም 10፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚሁ ቀን 10:30 ላይ ይታሸጋል፡፡
- ጨረታዉን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ግቢ/ዕ/ቤት/በብ/የሚ/የግ/ግ/ክ ቡድን ቢሮ ቁጥር 06 ጥር 19/2018 ዓ.ም በ3፡00 ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ በተገለጸበት ከ05 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 05 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በማስያዝ ውል መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን 20 በመቶ የመጨመርም የመቀነስም መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- መ/ቤቱ ጨረታውን በሚከፍትበት ቀን በዓል ፣ እሁድ እና ቅዳሜ ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ግብዓቱ የሚቀርበው በሙሉ ወይን ዉሃ ችግኝ ጣቢያ ሲሆን በሙያተኛ ተረጋግጦ ገቢ ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 06 ድረስ በአካል በመገኝት ወይም በስልክ ቁጥር 058 254 06 04 /09 10 62 76 34 በመደወል መረጃ ማግኝት ይችላሉ፡፡
የቢቡኝ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት

