ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
104

የጎንደር ከተ/ወረ/ፍርድ ቤት ግዠና ፋይናንስ ንብረት አስተዳዳር ቡድን በመ/ቤቱ ላሉ የስራ ሂደቶች ፤ ለአዘዞና ጠዳ ንኡስ ወረዳ ፍ/ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡ የተለያዩ እቃዎች እና አገልግሎቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡ ሎት 1.የደንብ ልብስ፣ ሎት 2. ከጥጥ የተሰራ ካፖርት ሸሚዝፕ፣ የዝናብ ልብስና ጥላ ፣ ሎት 3.የሀገር ውስጥ የሴትና የወንድ አጭር ቆዳ ጫማና ፕላስቲክ ቦት ጫማ ፣ ሎት 4. የጽህፈት መሳሪያዎች ወይም አላቂ እቃዎች ፣ ሎት 5.የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 6 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ሎት 7. የቢሮ ፈርኒቸር እቃዎች ፣ሎት 8. የህትመት ውጤቶችና ቲተሮች፣ ሎት 9. የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ጥገና የእጅ ዋጋ ግዥዎችን የሚከተሉትን መስፈርቶች ከሚያሟሉ አወዳድሮ መግዛት  ይፈልጋል፡፡

  1. ተጫራቾች በየሎቱ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና ያሳደሱ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ሰርተፍኬት አያይዘው የሚያቀርቡ፤ከ200,000.00/ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ለሚያቀርቡ ጠቅላላ ዋጋ ድምር እና ለኤሌክትሮኒክስ ነክ እቃዎች ደግሞ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡ የጨረታ ሰነዱ የሚሸጥበት ከሎት1. እስከ ሎት 9 የማይመለስ 00 /ሀያ ብር/ በመክፈል ጎንደር ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን  ቢሮ ቁጥር 5 በመቅረብ መግዛት ይቻላል፡፡
  2. ጨረታው በጋዜጣ አየር ላይ የሚቆየው ከህዳር 9 /2017 ዓ.ም እስከ ህዳር 23/ 2017 ዓ.ም  ድረስ  ይሆናል፡፡ ህዳር 24 /2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጐ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በግዥና ፋይናንስ አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡
  3. የሚገዙ አቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ ወይም ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በሎት ከሞሉት ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ ወይም ሲፒኦ ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ከመ/ቤቱ ግዥ እና ፋይናንስ ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 ከገንዘብ ያዥ በመ/ሂ 1 ለማስያዛቸው የገቢ ደረሰኝ ከሚወዳደሩበት ሰነድ ጋር ፎቶ ኮፒውን በማሸግ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሐሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ 2 ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ጎን/ከ/ወ/ፍ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 10 እስከ ህዳር 24/2017 ዓ/ም እስከ ጠዋቱ 3፡00 ድረስ ሰነዱን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ፡፡
  6. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ የእቃውን መጓጓዠ እና ማንኛውንም የመንግስት ታክስ ያካተተ ሆኖ መቅረብ አለበት፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል፡፡
  7. መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ መ/ቤቱ በሎት ድምር ወይም በነጠላ ዋጋ የማወዳደር መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. ተጫራቾች ያሸነፍትን እቃ ጎን/ከ/ወ/ፍ/ቤት ድረስ ማቅረብ አለባቸው ፡፡
  9. የሚጠገኑ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን የእጅ ዋጋ ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፤የሚጠገኑ እቃዎች የሚጠገኑበት ቦታ በማእከላዊ ጎን/ከ/ወ/ፍ በመ/ቤቱ ላሉ የስራ ሂደቶች እና ለአዘዞና ጠዳ ንኡስ ወ/ፍ/ቤቶች ይሆናል፡፡
  10. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በጎንደር ከ/ወ/ፍ ቤት የግዥ እና ፋይናንስ ንብረት አስ/ቡ/ቢሮ ቁጥር 10 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 126 00 36 በመደወል መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የጎንደር ከተማ /ወ/ፍርድ ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here