የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት የፍርን የመጀመሪያ ት/ቤት ማስፋፊያ ግንባታ ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ GC/BC የሆኑ ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተቋራጮች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
- በደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ በGC/BC ሥራ ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የነጋዴዎች መለያ ቁጥር የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት እና ወቅታዊ የሆነ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ሌሎች ለጨረታው አስፈላጊ የምትሏቸውን ሰነዶችን ማያያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠ/ዋጋ አንድ በመቶ በጥሬ ገንዘብ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባቸው፡፡
- የሞሉት ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ መሙያ ሰነዳቸውን ኦርጅናልና ኮፒ ብለው በተለያዩ ፖስታ ካሸጉ በኋላ በአንድ ትልቅ ፖስታ ሁሉንም ፖስታዎች አካቶ በማሸግ ፍ/ሠላም ከተማ አስተዳደር ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 43 ፊት ለፊት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት እስከ 11፡30 ድረስ ይቆይና በ22ኛው ቀን 4፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ጨረታውን ከመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ፍ/ሠላም ከተማ አስተዳደር ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 43 ከዋና ገ/ያዥ እጅ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለግንባታው የሚያስፈልገውን ማንኛውንም ቁሳቁስ እራሳቸውን ችለው የሚሰሩ ይሆናል፡፡
- በዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻለም፡፡
- ተጫራቸች ከአሁን በፊት የመንግስት ግዥዎች ላይ ተሳትፈው አሸናፊ መሆናቸው ተገልጾላቸው ውል ባለመያዛቸው ወይም በገቡት ውለታ መሠረት በአግባቡ ባለመፈፀማቸው እርምጃ ያልተወሰደባቸው መሆን አለባቸው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ሥርዝ ድልዝ ወይም ለመለየት አስቸጋሪ የሆነ የዋጋ አቀራረብ ከጨረታው ውጪ ያስደርጋል፡፡
- የጨረታው መክፈቻ ቀን አጋጣሚ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- በዚህ የግዥ ሂደት የሚነሱ አለመግባባቶች ወይም ያልተነሱ ነጥቦች 2003 ዓ.ም በወጣው የግዥ መመሪያ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
- ለበለጠ መረጃ ቢሮ ቁጥር 43 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 775 16 29 /883 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

