በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የጉና በጌምድር ወረዳ የክ/ድንጋይ ከተማ መሪ ማ/ቤት ለዲች ሥራ የሚውል ስሚንቶ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ጨረታ መሳተፍ የሚችሉ የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ያለባቸው፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ (ቲን) ቁጥር ያላቸው፡፡
- ያቀረቡት ዋጋ ከ200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆኑን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ግብር የከፈሉበት ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ አንድ በመቶ በሲፒኦ በባንክ በክ/ድንጋይ መሪ ማ/ቤት ስም ያስይዛሉ፡፡
- ከ1-5 የተዘረዘሩትን መረጃዎች ኮፒ ከጨረታ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ጨረታው ተጫረቾች (ህጋዊ ወኪሎቻው) በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 12 በ15ኛው ቀን 11፡30 ታሽጎ በቀጣዩ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
- የስሚንቶ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን ሥርዝ ድልዝ በሌለበት የተጫራቹን ስም፣ ፊርማ፣ ማህተም እና ጨረታ ያወጣውን መ/ቤት ስም እና አድራሻ በመግለጽ ከ2፡30 እስከ 11፡30 ክ/ድንጋይ ከተማ መሪ ማ/ቤት ባዘጋጀው ሳጥን ያስገባሉ፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ይቆያል፡፡ የአንዱን ኩንታል ዋጋ እና የጠቅላላ ዋጋ መግለጽ አለባቸው፡፡ የ1 ሰነድ ዋጋ ብር 400 (አራት መቶ ብር) ነው፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ ከተገለፀበት 5 ተከታታይ ቀናት በኋላ ክ/ድንጋይ መሪ ማ/ቤት ድረስ በመቅረብ የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መውሰድ አለበት፡፡
- ማ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- ስለጨረታው ተጨማሪ ማብራሪያ 09 18 71 44 11 መደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የክ/ድንጋይ ከተማ መሪ ማ/ቤት

