በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት በመደበኛ ካፒታል በጀት ለተሁለደሬ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ቢሮ ግንባታ የተቋራጭ ደረጃውን የሚያሟሉ የግንባታ ሥራ ተቋራጮችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
- ህጋዊ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
- ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- የግንባታ ተቋራጭ ደረጃቸዉ 4 እና ከዚያ በላይ የሆኑ፡፡
- የመልካም ስራ አፈፃፀም የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተዘረዘሩት መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውንና ተፈላጊ መረጃዎችን የዋጋ ማቅረቢያ ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በማለት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተቋራጮች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በጥሬ ገንዘብ በሲፒኦ ወይም (ቢድ ቦንድ) ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተቋራጮች የጨረታ ሰነዱን ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በጥሬ ገንዘብ ጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 6 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተቋራጭ በሚሞላ ዋጋ ላይ ሥርዝ ድልዝ ወይም አሻሚ የሆነ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ያልተሟላ ያቀርቡ እንደሆን ጨረታው ተቀባይነት የለዉም፡፡
- ተቋራጮች የዋጋ ማቅረቢያ በታሽገ ኢንቨሎፕ የማወዳደሪያ ዋጋቸዉ ኦርጅናል እና ኮፒ ማለት ማስታወቂያው ከወጣበት ከጥር 11/2018 እስከ የካቲት 09/2018 ዓ.ም 4፡00 ድረስ ተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 9 መ/ቤቱ ባዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ማስገባት አለባቸዉ፡፡
- ጨረታዉ የካቲት 9/2018 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ይክፈታል፡፡
- የጨረታ መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው በቀጣዩ የሥራ ቀን የመክፈቻ ሰዓትን ጠብቆ ይከፈታል፡፡
- ተቋራጮች የቢሮ ግንባታ ስራ አገልግሎት ዝርዝር ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ዉስጥ አንድ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋን እንድሁም ቀን ፈርማና የድርጅቱን ማህተም ማስፈር ይገባቸዋል፡፡
- የቋራጮች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትት ወይም የማያካትት መሆኑን መግለጽ አለባቸዉ፡፡
- በጨረታ ሂደቱ ላይ የ2014 የግንባታ መመሪያ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
- አሸናፊው የሚለየዉ በሎት ድምር ዋጋ ነው፡፡
- በሰነዱ የተዘረዘሩትን የግንባታ ሥራዎች ዋጋ በሙሉ ያልሞላ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ይሆናል፡፡
- አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ተጫራች መ/ቤቱ በጠየቀው መሰረት የመስራት ግዴታ አለበት፡፡
- ተቋራጮች የሞሉት ዋጋ ከመሃንድስ ግምት በላይ ከሆነ በመመሪያው መሰረት ጨረታው ውድቅ ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችለም፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሞከረ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ሆኖ ወደፊትም በመንግስት ጨረታ እንዳይሳተፍ ይደረጋል፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 033 222 00 12 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት

