የቋሪት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግ/ንብ/አስ/ቡድን ለ2018 በጀት ዓመት ለቋሪት ወረዳ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1. የጽ/መሳሪያ፣ ሎት 2. ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ሎት 3. የጽዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- ግዥው ከብር 200,000 (ሁለት ሽህ ብር) በላይ ከሆነ ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር በጥንቃቄ በስም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መገለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ቋሪት ወረዳ ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 05 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦርድ) ለሚወዳደሩበት የዕቃው ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በሲፒኦ ወይም በደረሰኝ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 (አስራ አምስት ) ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛው ቀን 3፡00 ይታሸግና በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት 3፡30 ይከፈታል፡፡ እለቱ በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተባለው ሰዓት ይታሸግና ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጽ/ቤቱ ከሚገዛው እቃ 20 በመቶ ጨምሮ ወይም ቀንሶ መግዛት ይችላል፡፡
- በዋጋ መሙያ ሰነድ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለ ተጫራቹ ፓራፍ ማድረግ አለበት፡፡
- በዚህ የጨረታ ማስታወቂያ ያልተካተቱ ህጎች እና ደንቦች በግዥ መመሪያው መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
- አሽናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 የስራ ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ በማቅረብ ውል መያዝ አለበት፡፡
- የውድድሩ ሁኔታ በጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ሞልቶ ካቀረበው ድርጅት ሲሆን ከአንድ ሎት ከፋፍሎ መሙላት ወይም መጫረት ከውድድር ውጭ ያስደርጋል፡፡
- አሸናፊው ያሽነፈውን ዕቃ ቋሪት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 4 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 12 46 02 26 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የቋሪት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

