ቁጥር አካ/ጥ/ግ/3/2018
የአብክመ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣንና ሀብት ስራ ማህበራት ኮሚሽን በመደበኛ በጀት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ የፅህፈት መሳሪያ፣ ፈርኒቸርና የመኪና ዲኮር እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ አግባብ ያለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ከጨረታው ሠነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ህጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ቁጥር፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- የጨረታውን ሠነድ ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ጋንቢ ጎን ካለው የአካ/ጥ/ባለስልጣን መ/ቤት አዲሱ ህንፃ ግራውንድ ላይ ግዥ ቢሮ በመምጣት 100 ብር በመክፈል መውሰድ ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች የጨረታው ሠነድ በሚጠይቀው መሠረት ሞልተው በታሸገ ፖስታ በማድረግ ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን እስከሚዘጋበት 3፡00 ድረስ ግዥ ቢሮ አጠገብ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
- በጨረታ መዝጊያው ቀን 3፡01 ታሽጐ 3፡30 ተጫራቶችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚያው ቀን በመ/ቤቱ ግዥ ቢሮ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በአል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰአት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ ሲፒኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ከ20 ሽህ ብር በላይ ለሆኑ ግዥዎች ቫቱን በግማሽ በመቶና ለአገልግሎት ግዥ 10ሺ ባላይ ለእቃ ግዥ ከ20ሺ በላይ ለሆኑ ግዥዎች ሶስት በመቶ ዊዝሆልዲንግ ታክስ ቢሮው ቆርጦ የሚያስቀር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- መ/ቤቱ አሸናፊውን ድርጅት በነጠላ ዋጋ የሚለይ ይሆናል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 320 62 06/09 11 59 75 82 ይደውሉ፡፡
የአብክመ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን

