የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ቡድን በ2018 በጀት ዓመት ለጓ/ሽ/ወ/ ሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የቢሮ ቁሳቁስ በግልጽ ጨረታ በጥቅል /በሎት/ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ ንግድ ፈቃድና የቲን ተመዝጋቢ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ስለ እቃው የተዘጋጀውን (ስፔስፊኬሽን) በትክክል በማጥናት በዋጋ ማቅረቢያ ሰነዱ ላይ የአንዱንና ጠቅላላ ዋጋ በትክክል መሞላት አለባቸው፡፡ ሥርዝ ድልዝ ያለበት ዋጋ ማቅረቢያ ተቀባይነት የለውም፡፡
- በዋጋው ማቅረቢያ ላይ የተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል ስም፣ ፊርማና የድርጅቱ አርማ ያለው ማህተም መኖር አለበት፡፡ በተጨማሪ በፖስታው ላይ ያጫራቹን መ/ቤት ስምና የራሳቸው አድራሻ በትክክል ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
- በሌላው ዋጋ ተንተርሶ መወዳደር አይፈቀድም፡፡
- የሞሉት ዋጋ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ፖስታዎች ላይ የንግድ አድራሻውንና ስሙን በመግለጽ በደንብ በታሸገ ፖስታ በማሸግ የሞላዉን ዋጋ ኦርጅናል ፖስታ የጓ/ሽ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ፋይናንስ ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ባዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ከቀረበዉ ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ የተመሰከረ (ሲፒኦ) ወይም በመሂ 1 በማስያዝ በፖስታዉ ዉስጥ አሽጎ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ከጨረታዉ ይሰረዛሉ፡፡
- በጨረታው ለተሸነፉ ተወዳዳሪዎች ያስያዙት ገንዘብ የጨረታው አሸናፊ ተለይቶ ውል ከወሰደ በኋላ ይመለስላቸዋል፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነታችውን ከተገለፀ በኋላ በሚቀጥሉት 5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉ 5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ የዉል ማስከበሪያ ካሸነፈዉ ከጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በመሂ 1 በማስያዝ ዉል መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- በጨረታ ውድድር ወቅት ቅር የተሰኘ ተጫራች አሸናፊው በተገለፀለት 5 የሥራ ቀናት ቅሬታውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ያለ በቂ ምክንያት ውሉን ካፈረሰ ያስያዘውን ገንዘብ በመቀጫ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡ በህግም እንዲጠየቅ ያደርጋል፡፡
- የጨረታው ሳጥን ከታሸገ በኋላ የሚቀርብ ጨረታ ውድድር ጥያቄ ወይም የማስተካከያ ተቀባይነት የለውም ማስተካከል የሚቻለው ጨረታው ከመከፈቱ 2 ቀን አስቀድሞ ማስተካከል ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ አስቀድሞ ከጨረታው መውጣት የሚችሉ ቢሆኑም ያስያዙት ገንዘብ አይመለስም፡፡
- በጨረታ ሰነዱ የተካተቱ ማንኛውም ሰነዶች ገንጥሎ ማስቀረት አይፈቀድም፡፡ ይህንኑ ችላ በማለት ተገንጥሎ የቀረበ የጨረታ ሠነድ ተቀባይነት የለውም፡፡ ለጨረታ መጓተት በር የሚከፍት በመሆኑ ያስያዘው ገንዘብ አይመለስም፡፡
- የጨረታ ሰነዱ 1 ገጽ መሆኑን ማረጋገጥ ከገዥ ይጠበቃል፡፡
- ጨረታው ከተከፈቱ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳችውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆኑ ለወደፊቱ በመንግስት የግዥ ጨረታ እንዳይሳተፍ እንደሚያደርግና ያስያዙት ገንዘብ እንደሚወረስ ማወቅ ይኖርባቸዎል፡፡
- ማንኛውም መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ለ15 ቀን ይቆያል፡፡
- ጨረታው በ16 ቀን 4፡00 ይዘጋና በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ 20 በመቶ የመጨመርም ሆነ የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታ ሠነዱን ቢሮ ቁጥር 06 በመምጣት ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መዉሰድ ይችላሉ፡፡
- የማስረከቢያ ቦታ ጓ/ወ/ ንብረት ክፍል ማስረከብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልገዎ በስልክ ቁጥር 058 229 00 50 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት

