የጎንደር ሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ክላስተር ማእከል ለማዕከሉ አገልግሎት የሚዉሉ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የኮምፒተር ዕቃዎች ሎት 3 የጽዳት ዕቃዎች፣ ሎት 4 የፈርኒቸር ዕቃዎች እንዲሁም ሎት 5 የመኪና መለዋወጫ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ተጫራቾች የሚከተለውን ማሟላት አለባቸው፡፡
- በዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 6,000 (ስድስት ሽህ ብር) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ማዘዣ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የተጨማሪ እሴት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታውን ሰነድ ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ገንዘብ ቤት የማይመለስ ብር 50 (ሀምሳ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ከጥር 25/2018 እስከ የካቲት 09/2018 ዓ.ም ለተከታታይ ቀን የሚቆይ ሲሆን የካቲት 10/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ጨረታው ታሽጎ ከረፋዱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማዕከሉ ግዥና ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሌላ ሰው ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይችሉም፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በማዕከሉ በግንባር በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 211 74 87 ወይም 09 18 03 23 67 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- አድራሻችን ጎንደር ቀበሌ 18 ከፍሎሪዳ ሆቴል ፊት ለፊት ወደ መስጊድ በሚወስደዉ መንገድ ከአቶ አብይ ምትኩ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- መ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የጎንደር ሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ክላስተር ማእከል

