የተስፋዬ ጌታቸው መታሰቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ የስራ ሂደት በ2018 በጀት ዓመት በመደበኛ እና በውስጥ በጀት ለሆስፒታሉ አገልግሎት የሚውሉ ሎት1. እስቴሽነሪ፣ ሎት2.የፅዳት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- ህጋዊ የታደሰ የዘርፉ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቲን ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ 200 ሽህ ብር በላይ ከሆነ ቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጧቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡20 ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ የድርጅቱን ማህተም፣ ስማቸውን፣ ፊርማቸውንና ሙሉ አድራሻቸውን በማስፈር የሞሉትን ሰነድና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን በፖስታ በማሸግ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የተስፋዬ ጌታቸው መታሰቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 04 ለስራው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- የጨረታው ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆኑና ለመደፊቱም በመንግስት የግዥ ጨረታ እንዳይሳተፉ ይደረጋል፡፡
- ተጫራቾች ለስራው የተዘጋጀውን ሰነድ የማይመለስ 50 ብር በመክፈል ዘወትር በስራ ስዓት ከተ/ጌ/መ/የመ/ደ/ ሆስፒታል ዋ/ገ/ያዥ ቢሮ ቁጥር 30 መግዛት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ከሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ አንድ በመቶ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ ነው፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኝም ይከፈታል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 667 06 35 ደውሎ ወይም ቢሮ ቁጥር 04 በአካል መጥቶመጠየቅ ይችላል፡፡
የተስፋዬ ጌታቸው መታሰቢያ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

