ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
153

የሰሜን ወሎ ዞን ፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት የግዥና ፍይናስ  ቡድን ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ አቅርቦቶች ማለትም ሎት 1 PPC ሲሚንቶ፣ ሎት 2 ጥራቱን የጠበቀ የግንባታ ድንጋይ እና ሎት 3 ጥራቱን የጠበቀ ንጹህ የወንዝ አሸዋ በግልጽ ጨረታ በሎት ድምር አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል:: ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾችን ማወዳደር ይፈልጋል::

በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው::

  1. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው::
  2. የግዥ አገልግሎት መጠን ከ200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ  /ቫት/ ከፋይነት የተመዝጋቡ መሆናቸውን ሊያረጋግጥ የሚችል  የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ::
  3. የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናሉንና ኮፒ በስም በታሸገ ፖስታ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
  4. የሚገዙ እቃዎች ዝርዝር መግለጫ /እስቴስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ::
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ እያንዳንዱ ሎት በማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ከገንዘብ ያዥ በመክፈል ሰነዱን መግዛት  ይችላሉ::
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ /የእቃውን የአገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ለፍ/ገ/ከ/አስ/ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት ህጋዊ ደረሰኝ መሂ ተቆርጦ ኮፒውን ወይም የጥቃቅን ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልግ የጨረታ የጥቃቅን ተጠቃሚ ከሆኑ ልዩ ድጋፍ ሰነዱ ጋር ማስያዝ አለባቸው::
  7. የጨረታ ሰነዱ የአየር ላይ ቆይታ 15 ተከታታይ ቀናት ሲሆን ከ30/07/2016 ዓ/ም እስከ 14 /08/2016 ዓ/ም እስከ ቀኑ 11፡30 ድረስ ሰነዱ ከፍላቂት ገረገራ ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት/ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ግዥ ቢሮ  መውሰድ ይቻላሉ::
  8. ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ሥራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን አስከ 16ኛው ቀን 3፡00 ድረስ በሳጥኑ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
  9. አንዱ ተጫራች በአንዱ ሎት ውስጥ የተዘረዘሩትን የእቃ አይነቶች መካከል ከፋፍሎ መጫረት አይችልም::
  10. እንደ በጀት አቅም ሃያ በመቶ የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው::
  11. በእያንዳንዱ ምድብ አሸናፊ የሚሆነው ድርጅት መስፈርቱን በሟሟላት ከጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ የሞላው ነው::
  12. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዌ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም በ16ኛው ቀን 3፡00 ተዘግቶ 3፡30 ይከፈታል::
  13. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በዚሁ ስዓት ተዘግቶ በዚሁ ስዓት ይከፈታል::
  14. አሸናፊ ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የሥራ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበርያ አስር በመቶ ለፍ/ገ/ከ;አስ/ገ/ኢ/ት/ጽ/ቤት በማስያዝ ውሉን መፈጸም ይኖርበታል:: በተባለው ቀን ውሉን የማይፈጽም ከሆነ ያስያዘው የውል ማስከበሪያ ለመንግስት ገቢ ይሆናል::
  15. አሸናፊው ውል ከፈጸመ በኋላ የአሸነፋቸውን እቃዎች በፍላቂት ገረገራ ከ/አስ/ ባሉት ቀበሌዎች ድረስ አጓጉዞ ያቀርባል\::
  16. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  17. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0332110528 እና በ0332110089 በመደወል ማግኝት ይችላሉ::
የፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here