ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
14

በአብከመ ጤና ቢሮ የደብረ ማርቆስ ደም ባንክ አገልግሎት ለጽ/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ብስኩት፣ የታሸገ፣ ውሃ የጽዳት እቃዎች፣ ህትመትና የጽ/መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙ እቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50 (ሃምሳ ብር) ብቻ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 1 ማግኙት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦርድ) የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንከ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በሰም በታሸገ ፖስታ በጽ/ቤቱ የግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ከየካቲት 02/2018 ዓ.ም እስከ የካቲት 16/2018 ዓ.ም ከ2፡30 እስከ 11፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በደብረ ማርቆስ ደም ባንከ የግ/ፋ/ንብ/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 የካቲት 17/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡30 ታሽጐ ከረፋዱ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. መስሪያ ቤቱ የጨረታውን 20 በመቶ የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. የጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡ ካለም ፓራፍ መደረግ አለበት፡፡
  13. የጨረታ መከፈቻው ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተገለፀው ሰዓት ይከፈታል፡፡
  14. የእቃውን ርክክብ በተመለከተ አሸናፊዉ ድርጅት ደብረ ማርቆስ ደም ባንከ አገልገሎት ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  15. የግዥው መጠን (ቫት) የሚገባ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢዎችንና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉትን ብቻ የሚጋብዝ ይሆናል፡፡
  16. ውድድሩ በድምር ወይም በሎት መሆኑን እንገልፃለን፡፡ በከፊል የጨረታ ሰነዱ ዝርዝር ላይ ዋጋ መሙላት ከጨረታ ውጭ ያስደርጋል፡፡
  17. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 1 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልከ ቁጥር 058 771 10 50 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የደብረ ማርቆስ ደም ባንክ አገልግሎት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here